ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማኅበረሰቡ ጤና አጠባበቅ የጤናና ጤና-ነክ መረጃዎች አዘጋገብና አቀራረብ ዙሪያ ከየካቲት 8-9/2014 ለሁለት ቀናት የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ለሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሰጥቷል፡፡

የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር አብድረሂም በድሩ በስልጠናው ላይ እንደገለፁት በአለምአቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ የሆነውን የኮረና/COVID-19/ ቫይረስ በተመለከተ ትክክለኛና ተገቢ የሆነ መረጃ ለማህበረሰቡ ተደራሽ ባለመደረጉ እ.ኤ.አ እስከ 2021 መጨረሻ ድረስ ብቻ ከ262 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች በቫይረሱ እንደተጠቁ እና ከዚህም ውስጥ ከ5 ሚሊየን በላዩ ለህልፈተ-ህይወት መዳረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም በሚዲያ የሚቀርቡ የጤናና ጤና-ነክ መረጃዎች በህብረተሰቡ ዘንድ አዎንታዊና አሉታዊ ተፅእኖ ስላላቸው የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች መረጃዎቹን በሚዘግቡበት ወቅት በጥንቃቄ እና ተገቢነት ባለው መልኩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በMedical Journalism እና Health Communication ዙሪያ ስልጠና የሰጡት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የእንግሊዘኛ ቋንቋና ስነ-ፅሁፍ መምህር የሆኑት መምህር ሬድዋን ነጃ የጤና መረጃ ከህብረተሰቡ የዕለት-ተዕለት ህይወቱ ጋር የተያያዘ ስለሆነ በጤናው ዘርፍ የሚዘገቡ መረጃዎች ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ሊሆን እንደሚገባና ህይወትን ለመታደግ ትክክለኛ መረጃ በትክክለኛ ሰዓትና ቦታ ለትክክለኛ አካል መቅረብ እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

ህብረተሰቡ ጤናውን በአግባቡ እንዲጠብቅና በሽታን አስቀድሞ የመከላከል ልምዱን ለማዳበር የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ወቅቱን የጠበቀ መረጃ ተደራሽ ማድረግ እንዳለባቸው መምህር ሬድዋን የገለፁ ሲሆን የማህበረሰቡን እውቀትና ግንዛቤ ለማሳደግና የባህርይ ለውጥ እንዲያመጣ ለማድረግ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

የጤናም ሆነ የሚዲያ ስራ ያለማህበረሰብ ተሳትፎ ውጤታማ ስለማይሆን ከጤና ጋር በተያያዘ የሚሰሩ የሚዲያ ስራዎች ውጤታማ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ጋር አብሮ የመስራት ልምድ ማዳበር እንደሚያስፈልግ መምህሩ አክለው ገልፀዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከስልጠናው ትልቅ ግብዓት እንዳገኙበትና በጤና ዘርፍ ላይ የበለጠ ስራ ለመስራት መነሳሳት እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል፡፡

በስልጠናው ላይ ከወልቂጤ ኤፍ.ኤም 89.2 ሬዲዮ፣ ከጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች፣ ከጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ፤ ከጉራጌ ዞን የጤና መምሪያ እንዲሁም ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት እና ከዩኒቨርሲቲው ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተወጣጡ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የካውንስል አባላት በዩኒቨርሲቲው የ2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ዙሪያ ተወያዩ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 1022 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT