ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...

የተማሪዎች ጥሪ ማስታወቂያ

በ2015 ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች

Read more ...

ለሁለተኛ ዙር GAT(Graduate Admission Test) አመልካቾች

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሁለተኛ ጊዜ የብሔራዊ  የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) በሚከተሉት መርሃ-ግብሮች ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን አስታውቋል።

Read more ...

 

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር፣ በምርምር እና ሆስፒታልን ጨምሮ እየሰጠ ያለውን ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ከትምህርት ሚኒስቴር የመጣው የሱፐርቪዢን ቡድን አሳስቧል።

የሱፐርቪዢን ቡድኑ ማሳሰቢያውን የሰጠው ሰሞኑን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከቀን 21/02/2016 ዓ.ም. ጀምሮ ባካሄደው የመስክ ምልከታ ማጠቃለያ ላይ በሰጠው ግብረ-መልስ ነው፡፡

የሱፐርቪዢን ቡድኑ በምልከታው የዩኒቨርሲቲውን ቤተሙከራዎች ፣ዲጂታል ቤተ-መፅሐፍት፣ የተማሪዎችን ማደሪያ፣ ዘመናዊ የምግብ ማብሰያ፣ ዘመናዊ የዳቦ መጋገሪያ ፣የመመገቢያ አዳራሾችን፣ የህጻናት ማቆያን፣ ስማርት የሆኑ የመማሪያ ክፍሎችን፣ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያን፣ የዳልጋ ከብቶች ምርምርና እርባታን፣ የፈረዝዬን የምርምር ጣቢያን ፣የወልቂጤ ዩኒቨርሰቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን፣በግንባታ ላይ የሚገኘውን የአስተዳደር ህንጻ፣ የማዕከላዊ ቤተ ሙከራ እና የአይሲቲ ኮምፕሌክስ ህንጻ ፕሮጀክቶችን ጎብኝቷል፡፡

የሱፐርቪዢን ቡድኑ በዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ የመማር ማስተማር ሂደት ዙሪያም የተማሪዎች ህብረት አመራሮችንና እና ተማሪዎችን ፣ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞችን እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን መካከለኛ እና ከፍተኛ አመራሮችንም አወያይቷል፡፡

ከምልከታው መልስ የሱፐርቪዢን ቡድኑ ለዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ግብረ-መልስ ያቀረበ ሲሆን በግብረ መልሱም ዩኒቨርሲቲው በመውጫ ፈተና ያስመዘገበው ውጤት እጅግ አበረታች መሆኑን፣ መምህራን በምርምር ስራ ተሳትፎ የሚያደርጉበት Institutional Research Information Management System ( IRIMS ) ሶፍትዌር ተግባራዊ መደረጉን፣በግቢው ውስጥ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት መኖሩን፣ የተደራጀ የቴክኖሎጂ ቤተ-ሙከራና ማሽኖች መኖራቸውና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እንዲጠቀሙበት ዕድል መሰጠቱን፣ ለመማሪያነት የሚያገለግሉ ስማርት ክፍሎች እና ዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት መኖራቸውን፣ በተማሪዎች ምግብ ቤት አካባቢ ያለው አሰራር በእጅጉ የሚበረታታ መሆኑን፣ የዋቤ አግሮ ኢንደስትሪ ጅምር ስራ እጅግ ተስፋ ሰጪ መሆኑን፣ ለመምህራን አቅም በፈቀደ መጠን የመኖሪያ ቤት መመቻቸቱን፣ግቢው ንጹህና አረንጓዴ መሆኑ እና የህጻናት ማቆያ ግንባታ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑ በጠንካራ አፈጻጸም አንስቷል፡፡

በቀጣይም ዩኒቨርሲቲው በመውጫ ፈተና ላይ ይበልጥ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባው፣ የዋቤ አግሮ ኢንደስትሪ ኢንተርፕራይዝን በሚገባ በማጠናከር በተለይም የወቅቱን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም እንዲረዳ የሰራተኛውን ኑሮ ማረጋጋት በሚችሉ ስራዎች ላይ በስፋት መሰራት እንዳለበት፣ በኢንተርፕራይዙ እየተመረተ ያለው የእንስሳት መኖ ምርት ወደ ማህበረሰቡ ተደራሽ በሚሆንበት መንገድ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ የሱፐርቪዢን ቡድኑ አሳስቧል፡፡

በመጨረሻም የተማሪዎች ቀለብ በጀትና የመምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ጥያቄ ሀገራዊና የሚታወቅ በመሆኑ መንግስት በጥናት ምላሽ እንዲሰጥበት ጉዳዩን ለትምህርት ሚኒስቴር እንደሚያቀርቡ ጠቁመዋል፡፡

በቀጣይም ዩኒቨርሲቲው የሱፐርቪዥን ቡድኑ የሰጠውን ግብረ መልስ በግብአትነት በመውሰድ የተሻለ ስራ እንደሚሰራ ያለውን የጸና እምነት ገልጿል፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 179 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2023. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT