ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...

የተማሪዎች ጥሪ ማስታወቂያ

በ2015 ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች

Read more ...

ለሁለተኛ ዙር GAT(Graduate Admission Test) አመልካቾች

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሁለተኛ ጊዜ የብሔራዊ  የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) በሚከተሉት መርሃ-ግብሮች ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን አስታውቋል።

Read more ...

 

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር ለስፖርት ሳይንስ ተማሪዎች እና ከዞኑ ለተውጣጡ የስፖርት ባለሞያዎች የአንደኛ ደረጃ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀምሯል::

የስልጠና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሃብቴ ዱላ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ምድብ ውስጥ መካተቱን ጠቅሰው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችም በሰለጠኑበት የትምህርት መስክ ተግባራዊ እውቀት ይዘው እንዲወጡ በሚያደርገው ጥረት የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር እንደሚጠይቅ ገልጸዋል፡፡

ምክትል ፕሬዝዳንቱ አክለውም የዚህ የተግባር ስልጠናም ዓላማ ተማሪዎች በንድፈ ሃሳብ የተማሩትን በተግባር እየቀየሩ ውጤታማ በመሆን በስራው አለም ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን እንዲሁም የዞኑ ስፖርት ባለሞያዎች ተግባራዊ የሆኑ ሳይንሳዊ ስልጠናዎች በመታገዝ የዞኑን ስፖርት የሚያሳድጉበት በመሆኑ አስፈላጊነቱ የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ሰልጣኞችም ስልጠናውን በአትኩሮት በመከታተል ተገቢውን እውቀት እንዲገበዩ ዶክተር ሃብቴ አሳስበዋል፡፡

የጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ አደም ሽኩር በበኩላቸው በዞኑ በቅርጫት ኳስ፣ የእጅ ኳስ እና በአትሌቲክሱ ዘርፍ ጉድለት የሚታይባቸው በመሆኑ ስልጠናው ክፍተቶችን በመሙላት የሰው ሃይል ለማሳደግ እንዲሁም ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል ሃላፊ የሆኑት ዶክተር አብድላዚዝ ሙሰማ ዩኒቨርሲቲው ከዞኑ ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በትብብር እየሰራቸው ያሉትን ስራዎች እንዲሁም ተቋሙ ያደረጋቸው ድጋፎች ላይ ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡

ስልጠናው የንድፈ-ሃሳብ እና የተግባር ሲሆን ለተከታታይ 13 ቀናት እንደሚቆይ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 222 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2023. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT