ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

ሙሉ ወጪው በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተሸፈነው፣ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ስነ–ጽሁፍ ትምህርት ክፍል መምህር በሆኑት በመምህር ካሚል ኑረዲን የተጻፈው እና በተለይም በጉራጊና ቋንቋ ሚስጥራት እና ተያያዥ እውነታዎች ላይ ትኩረት ያደረገው “መቅረዝ “ የተሰኘው መጽሀፍ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል ።

የምረቃ ስነስርዓቱ በአባቶች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሀብቴ ዱላ ባስተላለፉት መልዕክት መምህር ካሚል ኑረዲንን አመስግነው መጽሀፉ ለዚህ እንዲበቃ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት እገዛ ማድረጉን በመግለፅ በቀጣይም የጉራጊና ቋንቋን በማሳደግ ረገድ ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ የባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ክቡር አቶ ደግነህ ቦጋለ በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት የመፅሀፉን ደራሲ መምህር ካሚልን አመስግነው በክልሉ ውስጥ ያሉትን ቋንቋዎች እና ባህሎችን በማሳደግ ረገድ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የበኩሉን እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡

“መቅረዝ “ መጽሃፍ ለሰው ልጅ ትልቁ ጸጋ የሆነውን የቋንቋን ሁለንተናዊ ጉዳይ በስፋት እንደሚዳስስ፣ በተለይም የጉራጊናን ቋንቋ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የተለያዩ የመፍትሄ ሃሳቦችን በማመላከት ረገድ ሰፊ ድርሻ እንዳለው በፕሮግራሙ ላይ መጻፉን በዳሰሳ ያቀረቡት ዶክተር ፈቀደ ምኑታ ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ ዶክተር ጌታቸው ደዊ የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር የታሪክ፣ የቋንቋ እና የባህል መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ዶክተር መዘምር ተክለአብ ሰፊ ዳሰሳቸውን አቅርበዋል፡፡

መምህር ካሚል ኑረዲንም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተደረገላቸው እገዛ መጽሀፉ ለህትመት በመብቃቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው በተለያየ መልክ ድጋፍ ያደረጉትን አካላት በሙሉ አመስግነዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የካውንስል አባላት፣ የተከበሩ ወይዘሮ ልክነሽ ስርገማ የጉራጌ ዞን ዋና አፈጉባዔ፣ ክብርት ወይዘሮ መሰረት አመርጋ የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ፣ አቶ ቅባቱ ተሰማ የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር (ጉልባማ) ዋና ዳይሬክተር ፣ የዩኒቨርሲቲው መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች፣ ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች የተገኙ ሲሆን ለመድረኩ ድምቀት በመሳሪያ የተቀነባበረ ሙዚቃ በዩኒቨርሲቲው የሙዚቃ ትምህርት ቤት መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ግጥሞች እና መነባነብ ቀርቧል።

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 131 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT