ክፍት የሥራ ቦታ

ለስራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ

የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ከዚህ በታች ባለው ክፍት የስራ መደብ  ላይ ሰራተኞችን  አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡  

 የመምህራን ቅጥር (የቅጥር ሁኔታ በኮንትራት)

Read more ...

የፈተና ጥሪ ቁጥር ሰባት(7)

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመምህራንና የላብ ቴክኒሺያን ለመቅጠር በቀን 17/03/2015 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ የተመዘገባችሁና ቅድመ ምልመላ ያለፋችሁ አመልካቾች ከዚህ በታች

Read more ...

የፈተና ጥሪ ቁጥር ስድሰት (6)

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኢንተርፕራይዝ በክፍት ሥራ መደቦች በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ለፈተና የሚቀርቡ ተፈታኞች ዝርዝር

የፈተና ቀን 05/05/2015 ሠዓት ከጠዋቱ 3:00

Read more ...

ማስታወቂያ

ለነባር የክረምት ትምህርት ተማሪዎች በሙሉ

በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ በክረምት መርሀ-ግብር ትምህርታችሁን ለምትከታተሉ ነባር

Read more ...

ለሪሚዲያል (REMEDIAL) ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የሪሚዲያል (REMEDIAL)  ትምህርት ፈላጊዎችን ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

Read more ...

ለሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዳይሬክቶሬት በሥሩ ባሉት በCISCO እና በHuawei ዓለም አቀፍ አካዳሚዎቹ አማካኝነት ሥልጠናዎችን በማታ እና በሳምንቱ መጨረሻ (ቅዳሜና እሑድ) መርሐ ግብር በአነስተኛ ክፍያ ለመሥጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለዚህ ከዩኒቨርሲቲው ውጭ ያላችሁ የማኅበረሰብ አካላት በመመዝገብ ሥልጠናው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Read more ...

 

“ ውስጣዊ ግጭቶች እና የመቋቋሚያ ስልቶች ( Internal Conflicts and Coping Mechanisms in Ethiopia) ‘’ በሚል ርዕስና በተዛማች ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ከቀን 09-10/07/2014 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት ቆይታ የሚያደርገው ይህ 17ኛው ዓመታዊ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በይፋ ተጀምሯል፡፡

በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ባስተላለፉት መልዕክት በዓመታዊ ኮንፈረንሱ ለታደሙት ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን ካስተላለፉ በኋላ ዓመታዊ ኮንፈረንሱ በትክክለኛ ሰዓት ላይ የተካሄደ መሆኑን አስታውሰው በተለይም የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በኢትዮጵያ እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል፤በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመና አገራዊ ምክክር መድረክን የሚመራ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ለመጀመሪያ ጊዜ ባቋቋመበት ማግስት ይህ ዓመታዊ ኮንፈረንስ መካሄዱ ኮንፈረንሱን ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ዶክተር ፋሪስ አያይዘውም ሲገልጹ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ምንም እንኳን ከተቋቋመ አስር ዓመት የሞላውና በዕድሜው ብዙም ያልገፋ ተቋም ቢሆንም እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር በ2030 በኢትዮጵያ ከሚገኙ የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ቀዳሚ ሆኖ ለመገኘት ርዕይ ሰንቆ ተግቶ እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ መሰል ኮንፈረንሶችን የማዘጋጀት አቅሙን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ የመጣ መሆኑን ገልጸው ከዚህ ቀደምም የሚከተሉትን ኮንፈረንሶች 1) Crop Science Society of Ethiopia, 2) Ethiopian Physicists Association Conference, 3) The Grand Celebration of 55th World Theatre Day 4) the 2nd National Research Conference. ያዘጋጀ መሆኑን በማስታወስ ከእነዚህም ልምድ ወስዶ ይህንን ኮንፈረንስ በተሻለ መልኩ ለማዘጋጀት ጥረት ማድረጉን በስፋት አብራርተዋል፡፡

ፕሮፌሰር ጌትነት ታደለ የኢትዮጵያ ሶሲዮሎጂ ፤ ሶሻል አንትሮፖሎጂ እና ሶሻል ወርክ ባለሙያዎች (ESSSWA ) ማህበር ፕሬዝዳንት በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር ማህበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የአባላቱን ሙያዊ አቅምና ችሎታ በመጠቀም ለሀገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቶች የበኩሉን ሚና ሲጫወት መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ ፕሮፌሰር ጌትነት አያይዘውም ESSSWA በCOVID-19 ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ በተለይም በአዕምሮ ጤንነነትና በስነ ልቡና ድጋፍ ዙሪያ በሀገር ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉትና የችግሩ ሰለባ ለሆኑት የማህበረሰብ ክፍሎች ተገቢውን ድጋፍና ስልጠናዎችን በመስጠት የበኩሉን ወገናዊ ሃላፊነት ሲወጣ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡

ፕሮፌሰር ጌትነት ታደለ በተጨማሪ ሲገልጹ ESSSWA ከUSAID ጋር በአጋርነት በጋራ እየሰራ መሆኑን ገልጸው Social System Strengthening in Ethiopia (SSSE) የተሰኘውን ፕሮጀክት በ USAID የፋይናንስና ቴክኒካል ድጋፍ እየታገዘ ከቀድሞው Ministry of Labour and Social Affairs (MOLSA) , Ministry of Women , Children , Youth affairs (MoWCYA ), TVET agency እና TVET colleges ጋር በጋራ በመስራት ይህንን ፕሮጀክት በአራት ክልሎች ማለትም በአማራ፤ኦሮሚያ፤ጋምቤላና ደቡብ ክልል ላይ ተግባራዊ እንዲሆን በማድረግ ለወላጅ አልባ ህጻናትና በHIV/AIDS ለተጠቁ ወገኖች ዘርፈ ብዙ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን በስፋት አብራርተዋል፡፡

የክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ የሴቶችና የማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትርን መልዕክት በንባብ ያሰሙት ክቡር አቶ ጌታቸው በዳኔ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር “ ውስጣዊ ግጭቶች እና የመቋቋሚያ ስልቶች ( Internal Conflicts and Coping Mechanisms in Ethiopia) ‘ በሚል ለዚህ ዓመታዊ ኮንፈረንስ የተመረጠው ርዕስ በግልጽ የሚያሳየው የESSSWA ማህበርና አባላቱ ለኢትዮጵያ ሰላምና ለህዝቦቿ ደህንነት ያላቸውን ቁርጠኝነትና ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያሳዩትን የሁልጊዜም ዝግጁነት በግልጽ የሚያመላክት መሆኑን ገልጸው ለESSSWA እና ይህንን ዓመታዊ ኮንፈረንስ ላዘጋጁት አካላት ልባዊ ምስጋናቸውን ገልጸዋል፡፡

ከመክፈቻ ንግግሩ በኋላ ሁለት ጥናታዊ ጸኁፎች ማለትም “It Only Reopens Old Wounds” Lived Experiences of Amhara Survivors from the Miakadra Massaker in Ethiopia’’ (Adugna Abebe(PhD), The Reintegration challenges of internally Displaced Persons by Violent Ethnic Conflict in Dembya Woreda: Nort Western Ethiopia ( Getu Ambaye( PhD)) በሚል የቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ርዕሶች ላይም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ከጥናታዊ ጽሁፍ አቅራቢዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ቅድመ ገጽ

ስለ እኛ

የተማሪዎች ቅበላ

መማር ማስተማር

ምርምር

አገልግሎት

ተማሪዎች

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማሕበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር “Training on improving first aid support and injury prevention for teachers ,students and sport professionals” በሚል ርዕስ ያዘጋጀው ስልጠና ተሰጠ

Read more ...
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀውና በጉራጌ ዞን ስር በሚገኙ የመንግስት ሆስፒታሎች በነርሲንግ ሙያ ላይ ተሰማርተው ለሚያገለግሉ ባለሙያዎች “Improving Nursing Care Service through Timely ,Purposive and Integrated Nursing Round ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና ተሰጠ፡፡

Read more ...
በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለማህበረሰብ አገልግሎት የሚውል የተቀናጀ የዓሳ፣ ዶሮ እና የጓሮ አትክልት ልማት ስራ የርክብክብ መርሀ ግብር እና በዋቤ ችግኝ ጣቢያ ለክረምት አረንጓዴ ልማት የሚውሉ ችግኞች ዝግጅት የመስክ ምልከታ ተካሄደ

Read more ...
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ለሚገኙ ከ600 በላይ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የደብተር እና የእስክሪፕቶ ድጋፍ አደረገ

Read more ...
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስዊዘርላንድ ሀገር ከሚገኘው የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ ከሆነው Lucerne University of Applied Sciences ጋር ስልጠና ላይ መሰረት ያደረገ የተማሪዎች ለውውጥ ( Students Exchange) አደረገ

Read more ...
በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተከናወነ ያለው የችግኝ ተከላ በምሁር አክሊል

Read more ...

Competency Based Exit Exam Preparation & Implementation” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ስልጠና ለኮምፒዊቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ መምህራን ተሰጠ ፡፡

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በወልቂጤ ዩኒቪርሲቲ በአስ/ኮ/ማ/ም/ፕ/ጽ/ቤት በተማሪዎች ዲን ስር በሚገኘው የስፖርትና መዝናኛ ቢሮ አማካይነት ተዘጋጅቶ ከመጋቢት 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ሲካሄድ የቆየው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ለውስጥ ስፖርታዊ ውድድር በዛሬው ዕለት ግንቦት 12/2015 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ፍፃሜውን አግኝቷል ፡፡

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው “የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የውስጥ አሰራር ስርዓት መመሪያ” ዙሪያ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አሽከርካሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ሰራተኞች፣ የየኮሌጆች መምህራን እና ተማሪዎች አመታዊ የልዩ ልዩ ስፖርት ውድድር መካሄድ ጀመረ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሶስት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የክበባት እና ማህበራት የስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ

በመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ፣ በሰው ሀብት ልማት መመሪያ እና ደንብ ፣ በግዢ ሂደት አፈጻጸም ፣ በንብረት አስተዳደርና በፋይናንስ መመሪያ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ለዩኒቨርሲቲው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ፣ ቡድን መሪዎችና አስተባባሪዎች በመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ፣ በሰው ሀብት ልማት መመሪያ እና ደንብ ፣ በግዢ ሂደት አፈጻጸም ፣ በንብረት አስተዳደርና በፋይናንስ መመሪያ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

We have 391 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2023. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT