ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲና በዞኑ ትምህርት መምሪያ ትብብር በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ ያለው የማጠናከሪያ ትምህርት (ቱቶሪያል) የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ ተማሪዎችና ወላጆች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ገለጹ።ዶክተር ፋሪስ ደሊል ይህንን የገለጹት በጉራጌ ዞን በተለያዩ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የማጠናከሪያ ትምህርት (ቱቶሪያል) እየተሰጣቸው ያሉትን ተማሪዎችን በጎበኙበት ወቅት ነው፡፡

ዶክተር ፋሪስ በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለጹት ተማሪዎች ይህንን የተፈጠረላቸውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲጥሩ፣ሙሉ ጊዜያቸውን ለትምህርት እንዲያውሉ፣ ለትምህርት ልዩ ትኩረት እንዲሰጡና ነገን ተስፋ አድርግው በርትተው እንዲማሩ ልምዳቸውንም ጭምር በማካፈል የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

ዶክተር ፋሪስ አያይዘውም ለተማሪዎች ውጤታማነት የወላጆች ሚና ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸው ወላጆች ልጆቻቸውን በመቆጣጠር በመልካም ስነ ምግባር እንዲታነጹ በማድረግ በተለይም ወቅታዊ ውጤታቸውን በቅርበት እንዲከታተሉ አሳስበዋል ።

ዩኒቨርሲቲው በጉራጌ ዞን፣ በምስራቅ ጉራጌ ዞን፣ በየም ዞንና በቀቤና ልዩ ወረዳ በተመረጡ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተመሳሳይ የሆኑ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ዶክተር ፋሪስ ገልጸው በቀጣይ ዩኒቨርስቲው ያለውን የሰው ሀይልና ዕውቀት ተጠቅሞ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ የሚያደርገውን ሁለንተናዊ ተሳትፎ በሁሉም አካባቢዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለትምህርት ውጤት መሻሻል እንዲሁም የትምህርት መሰረተ ልማቶችን በማሟላት ረገድ መንግስትና ማህበረሰቡ እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ በትኩረት ከመደገፍ አንጻር ዩኒቨርሲቲው የበኩልን ድርሻ እንደሚወጣ ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወ/ማርያም በበኩላቸው እንደገለጹት የማጠናከሪያ ትምህርት (የቱቶሪያል እገዛው) ከመጀመሩ በፊት በፕሮግራሙ ለሚካፈሉት መምህራኖች ስልጠና መሰጠቱንና አስፈላጊ የሆነ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አስታውሰው ቱቶሪያሉ መምህራኖች ያላቸውን ዕውቀትና ልምድ ለተማሪዎች የሚያስተላልፉበት አጋጣሚ በመሆኑ የተማሪዎች ውጤትና ስነ ምግባር እንዲሻሻል በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል ።

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 279 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT