በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በትናንትናው ዕለት በይፋ ተመረቁ፡፡ የጨቅላ ሕጻናት ማዕከሉን እና ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ የመረቁት የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የማኔጅመንት አባላትና የቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ደጀኔ አየለ ሲሆኑ በተለይም የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከሉን አስመልክቶ የዩኒቨርሲቲው ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር በሆኑት በዶክተር አብዱረሂም በድሩ እና የህጻናት ስፔሻሊስት ሀኪም በሆኑት በዶክተር መሀመድ አማካይነት ለታዳሚዎች ሰፊ የሆነ ገለጻና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡