ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው “የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የውስጥ አሰራር ስርዓት መመሪያ” ዙሪያ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አሽከርካሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ኮርፖሬት ማኔጅመንት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር የሺሀረግ አፈራ ሲሆኑ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ እንደገለጹት መመሪያውን ማዘጋጀት ያስፈለገበት ምክንያት፡-

  1. በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተሽከርካሪዎች ስምሪትና አጠቃቀም አሰራር ውስጥ ያልተሸፈኑ ዝርዝር ጉዳዮች በሕግ ማዕቀፍ እንዲሸፈኑ በማድረግ መመሪያዉ በተሻለ ሁኔታ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችልበት ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፣
  2. ከተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲው ሊያጋጥመዉ የሚችለዉን አላስፈላጊ ወጪን ለመከላከል የሚያስችል ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓትን መዘርጋት በማስፈለጉ፣
  3. ከተሸከርካሪ አጠቃቀምና አያያዝ ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የስነ ምግባር ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ይህንን የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የውስጥ አሰራር ስርዓት መመሪያ ማዘጋጀቱንና በመመሪያው ዙሪያ ዋና ፈጻሚ ለሆኑት አሽከርካሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

መመሪያው ለአሽከርካሪዎቹ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን መመሪያውን መሰረት በማድረግ ከአሽከርካሪዎች ለተነሱት ጥያቄዎች በአስተዳደርና ኮርፖሬት ማኔጅመንት ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ደረጃ ምላሽ የሚሰጥባቸው ጉዳዮች በዕለቱ ምላሽ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በአንጻሩ በዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ደረጃ ምላሽ የሚሰጥባቸው ጉዳዮች በተዋረድ ለማኔጅመንቱ ቀርበው ምላሽ እንደሚሰጥባቸው በዕለቱ ተገልጿል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲው የተሽከርካሪ አያያዝን ለማዘመንና ወጪ ቆጣቢ የሆነ አሰራር ለመዘርጋት ለ24 ተሽከርካሪዎች ጂፒኤስ በማስገጠም አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን የዚህን ቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክቶ ያለውን አጠቃላይ መሻሻል ለመገምገም የተሞከረ ሲሆን ለተሸከርካሪዎቹ ጂፒኤስ በማስገጠም አገልግሎት መሥጠት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለነዳጅ በተጨማሪነት ሲወጣ የነበረ ብር 573,000 (አምስት መቶ ሰባ ሶስት ሺህ ብር) ለማዳን መቻሉ ተገልጿል፡፡ ይህ ከጅምሩ የሚበረታታ ተግባር እየተመዘገበበት ያለውን የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በዕለቱ ተገልጿል፡፡

በመጨረሻም አሽከርካሪዎች ለተገልጋዮች አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት አልፎ አልፎ በተወሰኑ አሽከርካሪዎች ዘንድ በሚስተዋሉት የስነምግባር ችግሮች ዙሪያ በስፋት ውይይት በማድረግ የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ ተችሏል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የካውንስል አባላት በዩኒቨርሲቲው የ2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ዙሪያ ተወያዩ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 922 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT