ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ ከአዕምሮ ጤና ጋር በተያያዘ በተለይም በአበሽጌ ወረዳ በሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ፣በዘርፉ በተሰማሩ የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች እና በማህበረሰቡ ተወካዮች ዘንድ ተገቢውን ግንዛቤ ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ ነው፡፡ በተጨማሪም በህመሙ ዙሪያ ዕውቀትን መሰረት ያደረገ የሃሳብ ልውውጥና የምክክር መድረክ በማድረግ ለማህበረሰቡ የጉዳዩን አሳሳቢነት እና ያሉትን ተግዳሮቶች ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ እንደሆነ የውይይት መድረኩን ካዘጋጁት ክፍሎች ለማወቅ ተችሏል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉት ከአበሽጌ ወረዳ የተውጣጡ የስነ-አዕምሮ ሀኪሞች፣ ዋና ዋና ፈጻሚዎች፣የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች፣ነርሶች፣በልዩ ልዩ የስራ ዘርፍ የተሰማሩ ሰራተኞች እና የማህበረሰብ መሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ በምክክር መድረኩ ላይ የተሳተፉት የባለድርሻ አካላት በአዕምሮ ጤና እክሎች ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ እና አጠቃላይ እይታ አስመልከቶ ያላቸውን ግንዛቤ በመድረኩ ላይ ገልጸዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የታወቁ የአዕምሮ ህመም ዓይነቶች ፣ምልክቶቹ እንዲሁም በግለሰብም ሆነ በማህበረሰብ ደረጃ የሚያሳድሩት ተጽዕኖ፣ ህመሙን እንዴት መለየት እንደሚቻል፣ ህመሙን ከጅምሩ መፍትሄ ለመስጠት ስለሚወሰደው አፋጣኝ እርምጃ አወሳሰድ ስልቶች እንዲሁም ህሙማኑን ከማግለል ይልቅ እንዴት አቅርበናቸው ተገቢውን የስነልቡና ድጋፍ መስጠት እና ወደጤንነታቸው እንዲመለሱ ማድረግ እንደሚቻል አስመልክቶ ሰፊ የሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶች ተካሂደዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመድረኩ የተለያዩ የዳሰሳ ጥናቶች የቀረቡ ከመሆናቸውም በላይ ማህበረሰብን ያማከለ የአዕምሮ ጤና ድጋፍ ማድረግን አስመልክቶ ሰፊ የሆነ እና ጠቃሚ ምክክር ተደርጓል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች በቡድን ሆነው የአዕምሮ ጤና ዕክል ከባህል አንጻር ያለውን እይታና የማህበረሰቡ መሪዎች ችግሩን በዘላቂነት ከመፍታትና ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ አንጻር ያላቸውን ሚና አስመልክቶ ጠቃሚ የሆነ ውይይት አድርገዋል፡፡

የዚህ ውይይት መድረክ ዋነኛ ተጠቃሚ የሚሆኑት በተለይም በአዕምሮ ጤና ዙሪያ በብዛት ወገኖቻቸው ተጠቂ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉት የጤና ባለሙያዎችና የማህበረሰብ መሪዎች ተገቢውን ዕውቀትና ክህሎት በመጨበጥ ከምክክር መድረኩ በኋላ ወደማህበረሰባቸው ሲመለሱ ለችግሩ ተጠቂ ለሆኑት አካላት ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ ለችግሩ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ከውይይት መድረኩ በሚገኘው ግንዛቤ መሰረት የውይይቱ ተሳታፊዎች ወደማህበረሰባቸው ሲመለሱ የህመሙ ተጠቂዎችን ከማግለል ይልቅ የማህበረሰቡ አንዱ አካል መሆናቸውን በመገንዘብ ለተሻለ ጤንነት በዘላቂነት ይሰራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚገልጹት የአዕምሮ ጤና ማለት አንድ ሰው ያለውን አቅም ለመጠቀም፣ በዕለት ተዕለት ኑሮው የሚያጋጥመውን ውጥረት ለመቋቋም እንዲሁም በሚኖርበት ማህበረሰብ ፍሬያማ አስተዋፅኦ ለማበርከት የሚያስችለው የስነ-ልቦና ሁኔታ ላይ መሆን ማለት እንደሆነ ይገልጻሉ። ይህ የስነ-ልቦና ሁኔታ ከተለመደው መስተጋብር ውጪ የሆኑ በአዕምሮ ላይ በሚፈጠሩ ጫናዎች ማለትም ባልተስተካከለ የትምህርት ወይም የስራ ሁኔታ፣ በቤተሰብ ውስጥ በሚፈጠሩ ችግሮች ብሎም በእርስ በርስ ግንኙነቶች ላይ በሚኖሩ ውጥረቶች ሊረበሽ እንደሚችልም አያይዘው ያስረዳሉ፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 258 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT