ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...

የተማሪዎች ጥሪ ማስታወቂያ

በ2015 ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች

Read more ...

ለሁለተኛ ዙር GAT(Graduate Admission Test) አመልካቾች

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሁለተኛ ጊዜ የብሔራዊ  የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) በሚከተሉት መርሃ-ግብሮች ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን አስታውቋል።

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማሕበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር “Training on improving first aid support and injury prevention for teachers ,students and sport professionals” በሚል ርዕስ ያዘጋጀው ስልጠና ተሰጠ

ስልጠናው የተሰጠው ለከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤት የስፖርት ሳይንስ መምህራን፣ የቀይ መስቀል ክበብ አባላት ተማሪዎች እና የስፖርት ባለሙያዎች ሲሆን ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሃንስ ገብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር የሚወስዱትን ሰልጠና በሰብዓዊነት እና በመልካም ፍቃደኝነት መርህ የሰውን ልጅ ህይወት ከሞት ከመታደግና እና የአካል ጉዳት እክሎችን ከመቀነስ አንፃር ስልጠናው ትልቅ አስተዋፅዖ ያለው በመሆኑ ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡

የስፖርት ሳይንስ ት/ት ክፍል ኃላፊ እና የፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር አብዱላዚዝ ሙሰማ በበኩላቸው እንደገለጹት ይህ ስልጠና ፋይዳው በት/ት ቤት ደረጃ የሚገኙ ተማሪዎችን ፣ስፖርተኞችን እና ማሕበረሰቡንም ጭምር ከመጥቀም አንፃር ከፍተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን አስታውሰው ተጎጂዎች ወደ ጤና ማዕከላት እስኪደርሱ ድረስ ከፍተኛ ጉዳት እንዳይደርስባቸው ባለሙያዎች ፍፁም በሆነ ሰብዓዊነት ድጋፍ መስጠት እንደሚገባቸውና ስልጠናውም ሰልጣኞችን ለዚህ ብቁ የሚያደርጋቸው መሆኑን በመግለፅ የስልጠናውን ዋና ግብ እና አላማዎችን በዝርዝር ገልጸዋል፡፡

የጉራጌ ዞን ቀይመስቀል ማሕበር ተወካይ እና አሰልጣኝ የሆኑት አቶ ሻሚል የሲሩ በበኩላቸው ይህ ስልጠና የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል መርሆዎችን መሰረት በማድረግ የሚሰጥ ፣ ደረጃውን የጠበቀ እና የሙያ እውቅና ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የሚያሰጥ ስልጠና በመሆኑ ሰልጣኞች በትኩረት ስልጠናውን እንዲከታተሉት በማሳሰብ በቀጣይ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር የሚሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና አለምአቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 113 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2023. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT