ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

ዩነቨርሲቲው የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ ከመሆኑ አንጻር በሚሰጣቸው የትምህርት ፕሮግራሞች እንዲሁም በሚያከናውናቸው የምርምር አጀንዳዎች የኢኮኖሚውን ውጤታማነት ለማሳደግ በተቀናጀ ሁኔታ ከተለያዩ የኢንደስትሪ ተቋማት ጋር በትስስር መሥራት ስለሚጠበቅበት ለዚህ ተግባር የሚያግዘውን የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው ዕለት ከተለያዩ የክልል ቢሮዎች፣ ከዞን መምሪያዎችና ከአምራች የኢንደስትሪ ተቋማት ጋር ተፈራርሟል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ባስተላለፉት መልዕክት የተዘጋጀው የምክክርና የመግባቢያ ስምምነት የመፈራረሚያ መድረክ በዩኒቨርሲቲው፣ በምርምር ተቋማት እና በኢንዱስትሪ መካከል አጋርነትንና ትብብርን ለማሳደግ፣የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ ፣ የትምህርትና የምርምር ጥራትን ለማሻሻል፣ ሀገራዊ የልማት አጀንዳዎችን ባገናዘበ መልኩ በቅንጅት፣ በወጥነት፣ በውጤታማነት እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ መሰረት ባደረገ መልኩ ለመስራት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የኢንደስትሪ ትስስርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ሃላፊ የተከበሩ አቶ ተሾመ ዳንኤል የከፍተኛ ትምህርት ፣ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፣ የምርምር ተቋማት እና የኢንደስትሪ ትስስር አዋጅ ቁጥር 1298/2023 አስመልክቶ ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ባቀረቡት ዝርዝር ማብራሪያ መነሻነት ከምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በተጨማሪም የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስ፣ ኢንፎርሜሽና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት የተከበሩ አቶ ሰላሙ አማዶ በበኩላቸው በተነሱት አስተያየቶች ላይ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም በቀጣይ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ አብረው ለመስራት ፍላጎታቸውን ካሳዩ የክልል ቢሮዎች፣ የዞን መምሪያዎች፣የቴክኒክና ሙያ ተቋማት እና ኢንደስትሪዎች ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የሚያስችል የስምምነት ሰነድ ዩኒቨርሲቲው የተፈራረመ ሲሆን የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች የምግብ ምህንድስና ላቦራቶሪን ጎብኝተዋል፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ

Read more ...

Wolkite University Senate, on its meeting held on July 2nd 2024, (Sene 25/2016 E.C.) discussed on the following two agendas

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የክረምት ችግኝ ተከላ መረሀ-ግብር በጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ጀመረ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የኢንደስትሪ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

Read more ...

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 227 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT