ድጋፉ የተደረገው በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኖሪያ ቤታቸው ለወደመባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሲሆን በዚሁ መሰረት ለቀቤና ወረዳ ነዋሪዎች 960 የቤት ክዳን ቆርቆሮዎችንና 240 ፓኬት ሚስማር ፣ለሙሁር አክሊል ወረዳ ነዋሪዎች 200 የቤት ክዳን ቆርቆሮዎችንና 50 ፓኬት ሚስማር ፣ ለእዣ ወረዳ ነዋሪዎች 840 የቤት ክዳን ቆርቆሮዎችንና 229 ፓኬት ሚስማር እና ለቸሀ ወረዳ ስጋ ደዌ ህሙማን 100 የቤት ክዳን ቆርቆሮዎችን በድምሩ 2100 የቤት ክዳን ቆርቆሮዎችን 519 ፓኬት ሚስማር ዩኒቨርሲቲው ድጋፍ ማድረጉን የዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር ክፍሌ ሌንቲሮ ገልጸዋል፡፡ ድጋፉ የተደረገላቸው ነዋሪዎችም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው ዩኒቨርሲቲው ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡