ህዝበ ድስኩሩን ያዘጋጀው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን በህዝበ ድስኩሩ ላይ ተገኝተው ድስኩር ያቀረቡት በኢሳት የቴሌቪዥን ጣቢያ በተንታኝነት የምናውቃቸው ዶክተር ታደሰ ብሩ ናቸው። የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና የአስተዳደር ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች እንዲሁም ከጉራጌ ዞን ጥሪ የተደረገላቸው የተመረጡ የወጣቶች ተወካዮች በህዝበ ድስኩሩ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
ዶክተር ታደሰ ብሩ እጅግ የሚደነቅ ስብዕና ፤ የዳበረ ሙያና የካበተ የመሪነት ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ የህዝበ ድስኩሩ ርዕስ “ከዩክሬን -ሩሲያ ግጭት የተማርነው እና የኢትዮጵያ ወጣቶች በሀገር ሰላምና ደህንት ዙሪያ ያላቸው ሚና “ የሚል ነበር፡፡
ህዝበ ድስኩሩን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ሲሆኑ እሳቸውም በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ እንደገለጹት ዶክተር ታደሰ ብሩ የዩኒቨርሲቲውን ጥሪ አክብረው በመገኘት በወቅታዊ ዓለማቀፋዊ ሁኔታ ከራሽያን እና የዩክሬን ጦርነትን የምንወስደው ተሞክሮ መነሻ በማድረግ የሀገራችን ወጣቶች በሰላምና ደህንነት የሚኖራቸውን ሚና ለታዳሚው ለማቅረብ ፈቃደኛ በመሆናቸው ያላቸውን ታላቅ ምስጋና አቅርበው ታዳሚውንም ጭምር ካመሰገኑ በኋላ የዶክተር ታደሰ ብሩን ልምድና ተሞክሮ በመግለጽ እጅግ ጠቃሚየሆነ መልዕክት የሚተላለፍበት መድረክ እንደሚሆን ያላቸውን ጽኑ ዕምነት ገልጸዋል፡፡
ዶክተር ታደሰ ብሩ እጅግ ሳቢና መሳጭ በሆነው ፅሁፋቸው እንደገለጹት ከዩክሬን -ሩሲያ ግጭት መማር የሚገባን መሰረታዊ ነጥብ በቂ የሆነ ትኩረት ተሰጥቶት መማር አለመቻላችን ገልጸው እየተካሄደ ያለው ጦርነት በዩክሬን -ሩሲያ መካከል ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ያካተተ እንደሆነና የወታደራዊ ኃይል ሚዛኑ ላይ ያለውን የዓለማትን ትኩረት መሰረት አድርጎ የተከፋፈለ መሆኑን በመግለጽ የጦርነቱም ጎራ በጂኦ ፖለቲካና በታክቲክ ላይ አትኩሮ የዓለማትን አሰላለፍ እንደለያየው ገልጸዋል፡፡ ስለሆነም እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ታዳጊ ሀገራት ከዚህ ጦርነት ዘርፈ ብዙ ልምድ ሊቀስሙ እንደሚገባ በዝርዝር ገልጸው ጦርነቱ በጥቅሉ ቅይጥ መሆኑን ጭምር ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ግጭትን መሰረት ያደረገውን የማህበረባችንን የአኗኗር ሁኔታ ለመቀየር፤ የማህበረሰባችንን የግጭት አፈታት ስልት በማሻሻል ወደ ተሻለ ሁኔታ ለማምጣትና ህዝቡን በተለይም ወጣቱን ያሳተፈ ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ለማስፈን ካሰብን በወጣቶች ላይ ሰፊ ስራዎችን መስራት እንደሚገባን ገልጸዋል፡፡
ዶክተር ታደሰ ብሩ ኢንተርዲሲፕሊነሪ ዶክትሬት ዲግሪ በማህበራዊ ሳይንስ፤ ማስተርስ ዲግሪ በምጣኔ ሀብት፤ ማስተርስ ዲግሪ በሰላም፣ በግጭት አፈታትና በዲፕሎማሲ ያላቸው አንጋፋ ምሁር ሲሆኑ ተጨማሪ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ግጭት አፈታት ከማማከር ስራቸው በተጓዳኝ በመስራት ላይ