በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች
እና በ2015 ዓ.ም ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በሪሚድያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2014 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር በውጤት እና በተለያዩ ምክንያቶች ዊዝድሮዋል (Withdrawal) በመሙላት ላቋረጣችሁ የዳግም ቅበላ (Readmission) ተማሪዎች በሙሉ፡-
የምዝገባ ጊዜ ህዳር 20-21/2016 ዓ.ም ሲሆን ትምህርት የሚጀመረው ህዳር 24/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ የሚከተሉትን ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡
1ኛ. መሰናዶ ያጠናቀቃችሁበትን ሰርተፍኬት፣ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውን ከማይመለስ አንድ ኮፒ ጋር እና አራት 3x4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ
2ኛ. አንሶላ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ መምጣት እንዳለባችሁ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡
ይህንን የመግቢያ ጊዜ አሳልፎም ሆነ ቀድሞ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት