ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















“ጉዞ ወደ አረንጓዴ ልማት” በሚል መሪ ቃል በጉራጌ ልማትና ባህል ማዕከል አማካይነት የተዘጋጀው 11ኛው ዙር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት በጉራጌ ዞን በአበሸጌ ወረዳ ጀጀባና ጋሶሬ ቀበሌ ከፌዴራል ፣ ከክልል፣ ከጉራጌ ዞን፣ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የተዉጣጡ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚኖሩ የብሔረሰቡ ተወላጆች እንዲሁም የቀበሌዉ ነዋሪዎች በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ ርስቱ ይርዳው ባስተላለፉት መልዕክት ለ11 ተከታታይ አመታት ሳይቋረጥና ከጊዜ ወደ ጊዜ ይበልጥ በተደራጀና በደመቀ ሁኔታ በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የሚገኙትን የዞኑ ተወላጆች እና የሌሎች አካባቢ ተወላጆች እያሰባሰበ በመከናወን ላይ ያለው የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ውጤታማነቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ክልል የግብርና ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ክቡር አቶ ኡስማን ስሩር በበኩላቸዉ ባስተላለፉት መልዕክት ግብርና የሀገራችን ትልቁ የዕድገት መሠረት መሆኑን ገልጸው የተፋጠነ ዕድገት ለማስመዝገብ ግብርናችንን ማዘመን እንደሚገባ እና ይህንንም እውን ለማድረግ የተፈጥሮ ሀብት ልማታችንን በአግባቡ በመያዝ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብራችንን በስፋት አጠናክረን መቀጠል እንደሚገባን አብራርተዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የአየር ንብረት መዛባት ከፍተኛ ዋጋ ከሚያስከፍላቸው ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን አስታውሰው የተፈጥሮ ሀብት አያያዛችንንና አጠቃቀማችን በማሻሻል ፣ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ በማልማት የአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ከፍ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሺሰማ ገብረስላሴ በበኩላቸዉ ማህበሩ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ሁለት እሴቶችን መሰረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸው የመላዉ ህዝብ የጋራ ፍላጎት ተብለዉ በተለዩ የልማት ስራዎች ለአብነት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ጅምር ስራዎች ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የባህል ማዕከል ግንባታ ፣የቡታጅራ ከተማ የዋና ጽህፈት ቤትና ቢዝነስ ማዕከል፣ በትምህርት በጤና በኑሮ ማሻሻል ፕሮግራምና በሌሎችም ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ ልማቶች በጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር አማካይነት እየተከናወነ እንደሆነም አብራርተዋል።

የችግኝ ተከላው መርሀ ግብር እንዲሳካ በማድረግ ረገድ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ላደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍና ዩኒቨርሲቲው ላበረከተው ትልቅ አስተዋጽኦ ከጉራጌ ልማትና ባህል ማዕከል የተዘጋጀውን የምስጋና እና የዕውቅና የምስክር ወረቀት ክቡር ዶክተር ፋሪስ ደሊል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ከሆኑት ከክቡር አቶ ርስቱ ይርዳው እጅ ተቀብለዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪም የፊታችን ሐምሌ 10 2015 ዓ.ም በአንድ ቀን 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተላለፈውን ሀገራዊ ጥሪ ዕውን ለማድረግ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ ያሳተፈ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ለማከናወን ሰፊ የሆነ ዝግጅት አድርጓል።

ከዚህም ባሻገር ዘንድሮ ለ3ኛ ዙር የሚካሄደውና 15 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የኬሮድ ታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫ “ለሰላማችን እንሮጣለን“ በሚል መሪ ቃል መነሻውን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መድረሻውን ወልቂጤ ከተማ በማድረግ በነገው ዕለት ይከናወናል፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

Wolkite University Public & International Relation Directorate

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ

Read more ...

Wolkite University Senate, on its meeting held on July 2nd 2024, (Sene 25/2016 E.C.) discussed on the following two agendas

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የክረምት ችግኝ ተከላ መረሀ-ግብር በጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ጀመረ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የኢንደስትሪ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

Read more ...

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 186 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT