መነሻውን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በማድረግ በወልቂጤ ከተማ የተካሄደው የ15 ኪሎ ሜትር 3ኛው ዙር የኬሮድ የጎዳና ላይ ታላቁ ሩጫ ውድድር መዳረሻውን ወልቂጤ በማድረግ በሰላም ተጠናቋል፡፡
ሩጫው ክብርት ዶክተር ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ገዛኸኝ አበራ ፣ ኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋ፣ አትሌት ሙክታር እድሪስ፣ አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ: አትሌት አየለ አብሽሮ እና ሌሎች ታላላቅ አትሌቶች በተገኙበት የተካሄደ ውድድር ነው፡፡ ዛሬ የተካሄደውን 3ኛውን ዙር የኬሮድ የጎዳና ላይ ሩጫ በተባባሪነት ያዘጋጀው ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡
ለጥበብ እንተጋለን!
We Strive for Wisdom!
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት