ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ጋአት ፋውንዴሽን፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እና የጉራጌ ዞን ትምህርት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማ/ኮሌጆች፣ ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂን እና ሰው ሰራሽ አስተውሎ (Artificial Intelligence) ለመተግበር የሚያግዙ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረጉ

የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ጋአት ፋውንዴሽን ፣የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እና የጉራጌ ዞን ትምህርት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ለሚገኙ 4 የኮንስትራክሽን እና ኢንደስትርያል ኮሌጆች፣ ለ10 የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ለ10 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂን እና ሰው ሰራሽ አስተውሎ (Artificial Intelligence) ለመተግበር የሚያግዙ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረጉ ፡፡

በድጋፍ አሰጣጡ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ እና የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅት መስራች የሆኑት ክቡር አምባሳደር ምስጋናው አርጋው ባስተላለፉት መልዕክት በህይወት ዘመናችን ያገኘነው ትልቅ ሀብት ትምህርት መሆኑን ፣ለትምህርት የምናጠፋው ጊዜ ተገቢ መሆኑን፣ለብዙ ጥፋቶቻችን መነሻው ትምህርት አለማግኘታችን መሆኑን ፣ በሰዎች መካከል ያለው ልዩነት አንዱ ጉዳይ በመማር እና ባለመማር መካከል ያለው ልዩነት መሆኑን፣ በበለጸጉትና ባልበለጸጉት ሀገራት መካከል ያለው ልዩነት በሳይንስ ፣ቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራዎች ጠንካራና ደካማ የመሆን እና ያለመሆን ልዩነት መሆኑን ፣ በትምህርት አማካይነት የችግር አፈታት አቅማችን ካደገ የትም መኖር እንደምንችል፣ በትምህርት ጥራት ላይ ስነሰራ አጠቃላይ የትምህርት ስነምህዳሩን ማሻሻል ብቻ ሳይሆን የማህበረሰብ ለውጥ ላይ ጭምር መስራት እንደሚገባን ገልጸው የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅትም ይህንን መሰረት በማድረግ በርካታ ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን በመግለጽ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በመሰል ተግባራት ላይ በመሳተፍ የሚጠበቅበትን ግዴታ ሊወጣ እንደሚገባ አጽንኦት በመስጠት አሳስበዋል፡፡

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል በበኩላቸው የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅትን እና ጋአት ፋውንዴሽንን አመስግነው የትምህርት ጥራትን ማሻሻል የህልውና ጉዳይ መሆኑን በመግለጽ እንደዚህ ዓይነት ድጋፎች በፈጠራው ስራ ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸውን ታዳጊዎች በእጅጉ ስለሚያበረታቱ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ሆኖም በሀገራችን ላለፉት በርካታ አመታት የተከተልነው የትምህርት ስርዓት እና የተገበረንብት መንገድ እጅግ የተሳካ እንዳልነበር አስታውሰው በ2014 የተመዘገበው 12ኛ ክፍል የሀገር-አቀፍ ፈተና የውጤት መዝቀጥ ጥሩ ማሳያ መሆኑና ገልጸዋል፡፡

ዶክተር ፋሪስ አያይዘው ይህ የትምህርት ዘርፍ ስብራት ለመጠገን በርካታ የሪፎም ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ለውጤታማነቱ ግን በመንግስት ብቻ ሳይሆን የብዙሀን ባለ ድርሻ አካላት ርብርብ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

ዶክተር ፋሪስ አያይዘውም ከዞኑ ሁሉም አካባቢዎች የተውጣጡ የአጠቃላይ ትምህርት ተማሪዎች በክረምት የፈጠራ ችሎታቸውን በSTEM (Science, Technology, Engineering and Mathematics) ቤተ- ሙከራዎች እያጎለብቱ መቆየታቸውን ገልጸው ከ2013 ጀምሮ STEM POWER የራሱን ማዕከል ከፍቶ የተለያዩ ተማሪዎችን በማዕከሉ በመቀበል የፈጠራ ልምምድ እንዲያደርጉ ብቻ ሳይሆን ተስፋ ሰጪ ጅምሮችም እየታዩበት መሆኑን አስታውሰው ለብዙ ወጣቶች አርዓያ የሆነውና የብዙ ፈጠራዎች ባለቤት ተማሪ ኢዘዲን ካሚልም የዚህ STEM POWER ፍሬ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የጋአት ፋውንዴሽን ተወካይ ባስተላለፉት መልዕክት የጋአት ፋውንዴሽን በአሜሪካን ሀገር በሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሆኑ የጉራጌ ተወላጆች አማካይነት የተቋቋመ ፋውንዴሽን መሆኑን ገልጸው የተመሰረተበት ዓላማ 1ኛ. የትምህርት ቤቶችን የማስፈጸም አቅም ለመገንባት 2ኛ. መምህራንን ለማሰልጠን 3ኛ ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድል ለመስጠት 4ኛ ኮዲንግን የአፍ መፍቻ ቋንቋ አድርጎ ለመጠቀም መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጉራጌ ዞን ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ አስከብር ወልዴ ባስተላለፉት መልዕክት የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ጋአት ፋውንዴሽን እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲን አመስግነው በተለይም የምስጋና ፋውንዴሽን በጉራጌ ዞን ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶችን በማስገንባት ትልቅ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጸው በዞኑ ደረጃ አስፈላጊው የትምህርት ፋሲሊቲ ወይም ግብአቶች በበቂ መልኩ ተሟልቶላቸው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ትምህርት ቤቶች 43% ብቻ በመሆናቸው ቀሪዎቹን የግብአት ችግር ያለባቸውን ለማጠናከር የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ጋአት ፋውንዴሽን እና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማ/ኮሌጆች፣ ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂን እና ሰው ሰራሽ አስተውሎ (Artificial Intelligence) ለመተግበር የሚያግዙ ቁሳቁሶችን መለገሳቸው እጅግ የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል የሚገባው ተግባር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም በጉራጌ ዞን ለሚገኙ 4 የኮንስትራክሽን እና ኢንደስትርያል ኮሌጆች፣ ለ10 የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ለ10 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂን እና ሰው ሰራሽ አስተውሎ (Artificial Intelligence) ለመተግበር የሚያግዙ ቁሳቁሶች ድጋፍ የተደረገ ሲሆን የምስጋና በጎ አድራጎት ድርጅት፣ጋአት ፋውንዴሽን ፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እና የጉራጌ ዞን ትምህርት ጽ/ቤት በቀጣይ በጋራ አብሮ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ከመፈራረማቸው ባሻገር በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ የዕለቱ የክብር እንግዳና የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች የSTEM ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ

Read more ...

Wolkite University Senate, on its meeting held on July 2nd 2024, (Sene 25/2016 E.C.) discussed on the following two agendas

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የክረምት ችግኝ ተከላ መረሀ-ግብር በጉራጌ ዞን እንደጋኝ ወረዳ ጀመረ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የኢንደስትሪ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

Read more ...

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 54 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT