የሰላም ስኬት የሚረጋገጠው የዜጎችን መሰረታዊ ፍላጎቶች በቻልነው ልክ ማሟላት ስንችል ነው በማለት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ገለጹ ፡፡
ዶክተር ፋሪስ ደሊል ይህንን የገለጹት “ ከበዓልም ማግስት እርዳታ ይሻሉ “ በሚል መሪ ቃል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የሰላም ፎረም አባላት ለቋሚ ተረጂዎች ባዘጋጁት የድጋፍ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው፡፡
ዶክተር ፋሪስ ደሊል በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ አያይዘው እንደገለጹት የዩኒቨርሲቲው የሰላም ፎረም አባላት ከተረጂ ወገኖቻችን ጋር እንድንገናኝ በጨቅላ እድሜያቸውና በልጅነት አቅማቸው አስበውና ተጨንቀው ይህንን የመሰለ ፕሮግራም ማዘጋጀታቸው እጅግ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ገልጸው በሀገራችን ውስጥ የሚስተዋለውን የወገኖቻችንን ችግር መፍታት የምንችለው ካለን አካፍለን አብረን መቆም ስንችል ብቻ ነው በማለት ገልጸዋል፡፡
ረ/ት ፕሮፌሰር መለሰ እጥፉ በበኩላቸው እንደገለጹት የዚህ ዓይነት በጎ ስራ በቀጣይ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የሰላም ፎረም ሰብሳቢ የሆነው ተማሪ አድነው ተስፋዬ በበኩሉ እንደገለጸው የሰላም ፎረሙ የግቢውን ውስጣዊ ሰላም ከማረጋገጥ ባሻገር ለተረጂ ወገኖችም በማሰብ ይህንን ፕሮግራም ለማዘጋጀት መቻሉን ገልጿል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ቁጥራቸው 40 ለሚሆኑ ተረጂዎች የዘይት፣ የዱቄት፣ ሳሙና እና የአልባሳት ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡
ለጥበብ እንተጋለን!
We Strive for Wisdom!
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት