የ2015 ዓ.ም. የመምህራን ፣ የአስተዳደር ሰራተኞች፣ የሪፈራል ሆስፒታል ሰራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የሚሳተፉበትና ከመጋቢት 23/2015 እስከ ግንቦት 05/2015 የሚካሄደው የውስጥ ለውስጥ ስፖርታዊ ውድድር ዛሬ በድምቀት ተጀምሯል፡፡
ውድድሩን በይፋ ያስጀመሩት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአስ / ኮ/ ማኔጅመንት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር የሻረግ አፈራ ሲሆኑ በመክፈቻው ፕሮግራም ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በዩኒቨርሲቲው የሚካሄደው ስፖርታዊ ውድድር ሀገራዊ አንድነትንና መግባባትን፣ ሁለንተናዊ ሰላምን ይበልጥ የሚያጠናክርና ፍጹም ስፖርታዊ ጨዋነት በተሞላው መልኩ ተጀምሮ መጠናቀቅ እንደሚገባው አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል፡፡
የኮምፒዊቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ፣ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ፣ የትምህርትና ስነባህሪ ኮሌጅ እና የህግ ትምህርት ቤት በውድድሩ መክፈቻ ላይ እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ለጥበብ እንተጋለን!
We Strive for Wisdom!
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት