ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ሶሲዮሎጂ ፤ ሶሻል አንትሮፖሎጂ እና ሶሻል ወርክ ባለሙያዎች (ESSSWA ) ጋር በመተባበር ያዘጋጁት 17ኛው ዓመታዊ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀመረ።

“ውስጣዊ ግጭቶች እና የመቋቋሚያ ስልቶች ( Internal Conflicts and Coping Mechanisms in Ethiopia) ‘’ በሚል ርዕስና በተዛማች ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ከቀን 09-10/07/2014 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት ቆይታ የሚያደርገው ይህ 17ኛው ዓመታዊ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በይፋ ተጀምሯል፡፡

በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ባስተላለፉት መልዕክት በዓመታዊ ኮንፈረንሱ ለታደሙት ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን ካስተላለፉ በኋላ ዓመታዊ ኮንፈረንሱ በትክክለኛ ሰዓት ላይ የተካሄደ መሆኑን አስታውሰው በተለይም የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በኢትዮጵያ እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል፤በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመና አገራዊ ምክክር መድረክን የሚመራ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ለመጀመሪያ ጊዜ ባቋቋመበት ማግስት ይህ ዓመታዊ ኮንፈረንስ መካሄዱ ኮንፈረንሱን ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ዶክተር ፋሪስ አያይዘውም ሲገልጹ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ምንም እንኳን ከተቋቋመ አስር ዓመት የሞላውና በዕድሜው ብዙም ያልገፋ ተቋም ቢሆንም እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር በ2030 በኢትዮጵያ ከሚገኙ የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ቀዳሚ ሆኖ ለመገኘት ርዕይ ሰንቆ ተግቶ እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ መሰል ኮንፈረንሶችን የማዘጋጀት አቅሙን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ የመጣ መሆኑን ገልጸው ከዚህ ቀደምም የሚከተሉትን ኮንፈረንሶች 1) Crop Science Society of Ethiopia, 2) Ethiopian Physicists Association Conference, 3) The Grand Celebration of 55th World Theatre Day 4) the 2nd National Research Conference. ያዘጋጀ መሆኑን በማስታወስ ከእነዚህም ልምድ ወስዶ ይህንን ኮንፈረንስ በተሻለ መልኩ ለማዘጋጀት ጥረት ማድረጉን በስፋት አብራርተዋል፡፡

ፕሮፌሰር ጌትነት ታደለ የኢትዮጵያ ሶሲዮሎጂ ፤ ሶሻል አንትሮፖሎጂ እና ሶሻል ወርክ ባለሙያዎች (ESSSWA ) ማህበር ፕሬዝዳንት በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር ማህበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የአባላቱን ሙያዊ አቅምና ችሎታ በመጠቀም ለሀገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቶች የበኩሉን ሚና ሲጫወት መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ ፕሮፌሰር ጌትነት አያይዘውም ESSSWA በCOVID-19 ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ በተለይም በአዕምሮ ጤንነነትና በስነ ልቡና ድጋፍ ዙሪያ በሀገር ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉትና የችግሩ ሰለባ ለሆኑት የማህበረሰብ ክፍሎች ተገቢውን ድጋፍና ስልጠናዎችን በመስጠት የበኩሉን ወገናዊ ሃላፊነት ሲወጣ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡

ፕሮፌሰር ጌትነት ታደለ በተጨማሪ ሲገልጹ ESSSWA ከUSAID ጋር በአጋርነት በጋራ እየሰራ መሆኑን ገልጸው Social System Strengthening in Ethiopia (SSSE) የተሰኘውን ፕሮጀክት በ USAID የፋይናንስና ቴክኒካል ድጋፍ እየታገዘ ከቀድሞው Ministry of Labour and Social Affairs (MOLSA) , Ministry of Women , Children , Youth affairs (MoWCYA ), TVET agency እና TVET colleges ጋር በጋራ በመስራት ይህንን ፕሮጀክት በአራት ክልሎች ማለትም በአማራ፤ኦሮሚያ፤ጋምቤላና ደቡብ ክልል ላይ ተግባራዊ እንዲሆን በማድረግ ለወላጅ አልባ ህጻናትና በHIV/AIDS ለተጠቁ ወገኖች ዘርፈ ብዙ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን በስፋት አብራርተዋል፡፡

የክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ የሴቶችና የማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትርን መልዕክት በንባብ ያሰሙት ክቡር አቶ ጌታቸው በዳኔ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር “ ውስጣዊ ግጭቶች እና የመቋቋሚያ ስልቶች ( Internal Conflicts and Coping Mechanisms in Ethiopia) ‘ በሚል ለዚህ ዓመታዊ ኮንፈረንስ የተመረጠው ርዕስ በግልጽ የሚያሳየው የESSSWA ማህበርና አባላቱ ለኢትዮጵያ ሰላምና ለህዝቦቿ ደህንነት ያላቸውን ቁርጠኝነትና ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የሚያሳዩትን የሁልጊዜም ዝግጁነት በግልጽ የሚያመላክት መሆኑን ገልጸው ለESSSWA እና ይህንን ዓመታዊ ኮንፈረንስ ላዘጋጁት አካላት ልባዊ ምስጋናቸውን ገልጸዋል፡፡

ከመክፈቻ ንግግሩ በኋላ ሁለት ጥናታዊ ጸኁፎች ማለትም “It Only Reopens Old Wounds” Lived Experiences of Amhara Survivors from the Miakadra Massaker in Ethiopia’’ (Adugna Abebe PhD), The Reintegration challenges of internally Displaced Persons by Violent Ethnic Conflict in Dembya Woreda: Nort Western Ethiopia (Getu Ambaye PhD) በሚል የቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ርዕሶች ላይም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ከጥናታዊ ጽሁፍ አቅራቢዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 519 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT