ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

በሴሚናሩ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራንን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲያችን የማኔጅመንት አባላት፣ የካውንስል አባላት፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡

ፕሮግራሙን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ባስተላለፉት መልዕክት የሀገርን ጥቅም የሚያስጠብቁ፣ለፈጣን ዕድገት ምቹ መደላድልን የሚፈጥሩ ሀገራዊ አጀንዳዎች በነጻ ውይይት በማዳበር እና በህዝባችን ዘንድ በማስረጽ ረገድ ሁሉም ዜጋ ሀገራዊ የሞራል ግዴታውን እንዲወጣ ለማድረግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ ሃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

ዶክተር ፋሪስ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲዎች የሀገራችን ምሁራን መፍለቂያ ማዕከል እንደመሆናቸው መጠን ለሀገራችን ብሎም ለመሪዎቻችን ግብዓት የሚሆኑ በሳልና በጥናት የተደገፉ ሀሳቦችን በማቅረብ ፣ የሀገራዊ ጥቅሞችን ሊያስከብሩ የሚችሉ አስተሳሰቦችን በህዝባችን ዘንድ በማስረጽ፣ በህብረተሰባችን ዘንድ የጋራ መግባባትን በመፍጠር እና ለትግበራው ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ በማድረግ ረገድ የተቋማት ሚና የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዶክተር ፋሪስ አክለውም ለዘመናት የህዝባችን ጥያቄ የሆነውና በተለይም ከኤርትራ መገንጠል ማግስት ጀምሮ ምላሽ ያላገኘው የባህር በር (የወደብ) ጥያቄን ፍጹም ሰላማዊና ዓለም አቀፍ ህጎችን መሰረት ባደረገ መልኩ ለመፍታት መንግስት ከፍተኛ የሆነ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውሰው የባህር በር ጉዳይ የመንግስት ሀሳብ ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ጉዳይ እንደሆነ በመገንዘብ የባህር በር እንዴት ? ከየት? መቼ? ወዘተ.. በሚሉ ሃሳቦች ላይ ምክክር ማድረግ እጅግ አስፈላጊ በመሆኑን ገልጸው ይህ መድረክ መዘጋጀቱን ዶክተር ፋሪስ ደሊል በንግግራቸው ላይ አብራርተዋል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይ የምሁራንን እይታ መሰረት ያደረጉ ጥናታዊ ጽሁፎች በዘርፉ ባለሙያዎች አማካይነት ለተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ ትኩረት የተደረገባቸው ዋና ዋና ነጥቦች ፡-

v ኢትዮጵያና የባህር በር ታሪካዊ ዳራ

v የባህር በር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ

v የባህር በር ባለቤትነትና የፍትሀዊ ተጠቃሚነት መብት ከዲፕሎማሲና ከዓለም አቀፍ ህጎች አንጻር

v የባህር በር ባለቤትነትና ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንጻር የሚዲያዎች ሚና የሚሉ ሲሆን በውይይት መድረኩ ላይ የመወያያ ጽሁፎቻቸውን ያቀረቡት

1ኛ) አቶ በቃሉ ዋቺሶ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ

2ኛ) አቶ እንዳለ ንጉሴ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ

3ኛ) ዶክተር አብድላዚዝ ዲኖ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

ሲሆኑ በዚህ ወቅታዊና ሀገራዊ በሆነው አጀንዳ ላይ ምሁራዊ ትንታኔ አቅርበዋል፡፡

በጽሁፍ አቅራቢዎቹ በስፋት እንደተገለጸው ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ አካባቢ ካላት የጂኦ- ፖለቲካዊ አቀማመጥ፣ በየጊዜው እያሳየች ካለቸው የኢኮኖሚ አቅም ዕድገት እና ካላት የህዝብ ብዛት አንጻር በቀጠናው አዎንታዊ ተጽዕኖ የመፍጠር አቅም ያላት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው በአንጻሩ ግን ወደብ አልባ ሀገር ከመሆኗ የተነሳ የወደብ ባለቤት በሆኑ የጎረቤት ሀገራት ላይ ጥገኛ በመሆን ወደ ውጭ ለምትልካቸው ምርቶችም ሆነ ወደ ሀገር ውስጥ ለምታስገባቸው ሸቀጦች ለወደብ ኪራይ ከፍተኛ የሆነ መዋዕለ-ንዋይ በማፍሰስ ላይ የምትገኝ በመሆኗ ይህ ሂደት በኢኮኖሚ አቅሟ ላይ ግዙፍ ሊባል የሚችል አሉታዊ ተጽዕኖ እየፈጠረባት እንደሚገኝ የጽሁፍ አቅራቢዎቹ አብራርተው ኢትዮጵያ አሁን ላይ እያቀረበች ያለቸው የወደብ ተጠቃሚነት ጥያቄ ተገቢነትና ህጋዊ መሰረት ያለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጽሁፍ አቅራቢዎቹ ባቀረቡት የመወያያ መነሻ ጽሑፍ ላይ ከተሳታፊዎች ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ውይይት ይካሄድባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 365 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT