ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

የእውቅና መድረኩን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ባስተላለፉት መልዕክት ለተመዘገበው ውጤት መሳካት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ፣ለተሻለ ውጤት መምጣት ሌት ተቀን ለፍታችሁ አስደሳች የሆነ ውጤት እንዲመዘገብ ላደረጋችሁ ሁሉ ፣ዛሬ ላይ በኩራት ይህንን ውጤት ለመዘከር ላበቃችሁን ለሁሉም የባለድርሻ አካላት በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የሀገራችንን የትምህርት ጥራት ስብራት ለመጠገን መንግስት ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎችን እየተገበረ መሆኑን ዶክተር ፋሪስ ገልጸው ለዓመታት የነበረው የምዘና ስርዓታችንን ለማስተካከል፣ ተማሪዎች ከኩረጃ በጸዳ ሁኔታ በራስ የመተማመን ብቃታቸውን በመጨመር ፣በየተቋማቱ የሚታየውን የምዘና ወጥነት ለማስተካከል እና በሀገራዊ ስታንዳርድ መመዘኛ መሰረት ተማሪዎችን ለማብቃት የመውጫ ፈተና መዘጋጀቱን ዶክተር ፋሪስ ገልጸዋል፡፡

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲም የጤና ሳይንስ ኮሌጅን ሳይጨምር በ43 ፕሮግራሞች በመደበኛ ፕሮግራም ካስፈተናቸው ተማሪዎች 79.6 በመቶ ማሳለፍ መቻሉን ዶክተር ፋሪስ ገልጸው ውጤቱ ከሀገራዊ አማካዩ ማለትም ከ62.3 በመቶ አንጻር እና ከበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነጻጸር የላቀና እጅግ ተስፋ ሰጪ ውጤት መሆኑን ገልጸው በዚህ ውጤት ያኮራችሁን የቀድሞ ተማሪዎች፣ ለውጤቱ መሳካት ሙሉ አቅማችሁን የተጠቀማችሁ መምህራን እና በሁሉም እርከን ያላችሁ የዩኒቨርቲያችን አመራሮች እና የተቋሙ የቀድሞ አመራሮች ጭምር ልፋታችሁ ፍሬ ስላፈራ ልትኮሩ ይገባል በማለት የሞቀ ደስታቸውን ገልጸዋል ፡፡

ዶክተር ፋሪስ በንግግራቸው ማጠቃለያ ላይ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች በጥሩ ውጤት ያስመረቅናቸውን እንቁ ተማሪዎችን ወኔ ሰንቀው እነሱን እንደተምሳሌት በመውሰድ ለአፍታም ሳይዘናጉ ሁሌም በማጥናት ዳግም በልፋታቸው ኮርተው ዩኒቨርሲቲውን እንዲያኮሩ ፣ መምህራንም በዘንድሮው ዓመት ከአምናው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ተግተው እንዲሰሩ፣ በየደረጃው ያለው አመራሩም ዛሬም ነገም የአመራር ጥበቡን ፣ ጥረትና ጥንካሬውን እንዲያስቀጥል አደራቸውን ገልጸዋል፡፡

ከዶክተር ፋሪስ የመክፈቻ ንግግር በኋላ በ2015 ዓ.ም. በሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አፈጻጸም የጥናት ውጤት በዝርዝር ቀርቦ በቀረበው ጥናት ዙሪያ የተለያዩ ጠቃሚ ሀሳቦች ተነስተው የጋራ ውይይት ተደርጎበታል ፡፡

በተመዘገበው አጠቃላይ አፈጻጸም ካሉት ኮሌጆች መካከል ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት ፡-

1ኛ) የግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ

2ኛ) የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ

3ኛ ) የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡

በመጨረሻም ከፍተኛ የሆነ ውጤት ላስመዘገቡ ኮሌጆች እና የትምህርት ክፍሎች ሽልማት እና የምስክር ወረቀት ከመሰጠቱም በላይ ለዚህ ውጤት ከፍተኛውን ድርሻ ለሚወስደው ለዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንትም እውቅና ተሰጥቷል፡፡

የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ብቁ የሰው ሃይል በማዘጋጀት ወደ ኢኮኖሚ መግባቱን ማረጋገጫው አንደኛው መንገድ ሲሆን ተመራቂዎች በተማሩበት ሙያ ዘመኑ የሚጠይቀውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ገንብተው ስለመውጣታቸው የሚመዝን ከመሆኑም ባሻገር ዲግሪ በያዙ ተመራቂዎች መካከል በብቃት የሙያውን ምሉዕነት ተላብሶ የተመረቀው የትኛው እንደሆነ ለመመዘን የሚያስችል ከጥራት ማረጋገጫ መሳሪያዎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በዓለም አቀፍ የትምህርት ተቋም አማካይነት ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የአመራርነት ስልጠና መሰጠት ጀመረ

Read more ...

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 314 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT