ክፍት የሥራ ቦታ

ለስራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ

የወልቂጤ ዩንቨርስቲ ከዚህ በታች ባለው ክፍት የስራ መደብ  ላይ ሰራተኞችን  አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡  

 የመምህራን ቅጥር (የቅጥር ሁኔታ በኮንትራት)

Read more ...

የፈተና ጥሪ ቁጥር ሰባት(7)

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመምህራንና የላብ ቴክኒሺያን ለመቅጠር በቀን 17/03/2015 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ የተመዘገባችሁና ቅድመ ምልመላ ያለፋችሁ አመልካቾች ከዚህ በታች

Read more ...

የፈተና ጥሪ ቁጥር ስድሰት (6)

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኢንተርፕራይዝ በክፍት ሥራ መደቦች በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ለፈተና የሚቀርቡ ተፈታኞች ዝርዝር

የፈተና ቀን 05/05/2015 ሠዓት ከጠዋቱ 3:00

Read more ...

ማስታወቂያ

ለነባር የክረምት ትምህርት ተማሪዎች በሙሉ

በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ በክረምት መርሀ-ግብር ትምህርታችሁን ለምትከታተሉ ነባር

Read more ...

ለሪሚዲያል (REMEDIAL) ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የሪሚዲያል (REMEDIAL)  ትምህርት ፈላጊዎችን ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

Read more ...

ለሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዳይሬክቶሬት በሥሩ ባሉት በCISCO እና በHuawei ዓለም አቀፍ አካዳሚዎቹ አማካኝነት ሥልጠናዎችን በማታ እና በሳምንቱ መጨረሻ (ቅዳሜና እሑድ) መርሐ ግብር በአነስተኛ ክፍያ ለመሥጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለዚህ ከዩኒቨርሲቲው ውጭ ያላችሁ የማኅበረሰብ አካላት በመመዝገብ ሥልጠናው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Read more ...

 

በጀፚረ ቅርስ አጠባበቅ ዙሪያ በሀገር በቀል ዕውቀት ልማት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀው የምክክር መድረክ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ፡፡ “ጀፚረን የመሰሉ እንቁ ቅርሶቻችንን ተንከባክበንና ጠብቀን ለትውልድ እናስተላልፍ” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ የምክክር መድረክ ላይ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ተወካይ፣የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ፣ የጉራጌ ዞን የሴቶች ወጣቶችና ህጻናት መምሪያ ሀላፊ፣ በጉራጌ ዞን ከሚገኙ 16 ወረዳዎች የተውጣጡ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ሃላፊዎች፣ የጉራጌ የባህል ሸንጎ አባላት እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በምክክር መድረኩ ላይ ተሳትፈዋል፡፡

የምክከር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ሲሆን ዶክተር ፋሪስ በንግግራቸው ላይ እንደገለጹት ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት አካል በሆነው የሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው በጥናትና ምርምር ተለይተው ከሚሰሩ የማህበረሰብ አገልግሎቶች አንዱ የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ዶክተር ፋሪስ አያይዘውም የጉራጌ ማህበረሰብ እንደሌሎች የሀገራችን ህዝቦች ሁሉ የአኩሪ ባህል ባለቤት መሆኑን አስታውሰው ከእነዚህም አኩሪና ከሚዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች መካከል አንዱ ጀፚረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ጀፚረ ከዘመናዊ ምህንድስና የማይተናነስ በመንደሮች መካከል የሚያልፍ ግርማ ሞገስን የተላበሰ ጥበብ መሆኑን ዶክተር ፋሪስ በንግግራቸው ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ዶክተር ፋሪስ እንደገለጹት በጉራጌ ታሪክ ጥንት መሬት የሚከፋፈለው በዘፈቀደ ሳይሆን በባህሉ በተመረጡ አባቶች እና የመሬት ልኬት ዳኞች አማካይነት መሆኑን ገልጸው “ጎጎት” መጽሀፍን ዋቢ በማድረግ እንደገለጹት ጀፚረ ስፋቱ12 ዘንግ መሆኑንና ርዝመቱ ግን በመሀል የሚያልፍ ወንዝ ፣ ገደል ወይም ደን እስከሌለ ድረስ ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

ዶክተር ፋሪስ በተጨማሪ እንደገለጹት ጀፚረ የለቅሶ ስርዓት የሚፈጸምበት፣እግረኛና ፈረሰኛ ሙሾ የሚደረድርበት፣የሰርግ ስነስርዓት ሲኖር የሙሽሪትና የሙሽራ አጃቢ ወገኖች በዘፈንና በግጥም የሚሞጋገሱበትና በሽማግሌዎች የሚባረኩበት፣ሙሽሮች አጋጌጣቸው የሚታይበትና ውበታቸው ጎልቶ የሚወጣበት፣በእናቶችና አባቶች የሚመረቁበት፣ሕጻናት እንዳሻቸው የሚቦርቁበት ፣ ጎረምሶች የገና ጨዋታ የሚጫወቱበት፣ ዳመራ የሚደመርበት፣ወጣቶች የፈረስ ጉግስ የሚለማመዱበት፣ በቅሎና ፈረስ የሚገራበት፣ኮርማዎች እርስ በርሳቸው የሚፈታተሹበትና የሚያጓሩበት እንዲሁም ሽማግሌዎች ባህላዊ ዳኝነት የሚያካሂዱበት መሆኑን በዝርዝር ገልጸዋል፡፡ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲም ለዚህ ታሪካዊ ቅርስ ትልቅ ቦታ በመስጠት ጀፚረ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅናን እንዲያገኝ በማሰብ ፡-

1ኛ) በዩኒቨርሲቲው ማስተር ፕላን ላይ ጀፚረ በዲዛይን መካከተቱን

2ኛ) ጀፚረንዳ በሚል ስያሜ በወልቂጤ ኤፍ ኤም 89.2 ሬዲዮ በሳምንት ሁለት ቀን የሚተላለፍ ፕሮግራም መጀመሩን

3ኛ) በቀጣይ ዓለም አቀፍ ስርጭት ሊኖረው የሚችል “ Jofere Ethiopian Journal of Applied Sciences” የሚል የጆርናል ህትመት ለማስጀመር በዩኒቨርሲቲው ሴኔት መጽደቁን

4ኛ) የዩኒቨርሲቲው ሎጎ ሙሉ በሙሉ ጀፚረን የሚገልጽ መሆኑን ዶክተር ፋሪስ በዝርዝር ገልጸው ይህ እንቁ የሆነው ቅርስ ለተለያዩ ሰው ሰራሽ አደጋዎች መጋለጡን በማስታወስ ይህንን መነሻ አድርጎ ዩኒቨርሲቲው የምክክር መድረኩን ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ ከዶክተር ፋሪስ ደሊል የመክፈቻ ንግግር በኋላ “Tracing Jefore’s Features, Provisions, intervention and Restoration” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሁፍ በዩኒቨርሲቲው የSociology ትምህርት ክፍል መምህር በሆኑት በመምህር አብነት ሺፈራው የቀረበ ሲሆን በቀረበው ጥናታዊ ጽሁፍ ላይ ሰፋ ያሉ ውይይቶች ተካሂደውበታል፡፡

በምክክር መድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደተገለጸው ጀፚረ እጅግ አሳሳቢ በሆነ ደረጃ ላይ ስለሚገኝ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ሊደረግለት እንደሚገባ፣ የጉራጌ ማህበረሰብ የጀፚረ ባለቤት ስለሆነ ጀፚረን ሊንከባከበው እንደሚገባ፣ የባህል ሸንጎ አባላቶቻችን በትኩረት መስራት እንዳለባቸው፣የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን ጀፚረን በባህላዊ ቅርስነት በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ጥረት ቢደረግ፣ለጀፚረ ዕውቅና ሊሰጠው እንደሚገባ፣ ጀፚረን በተስተካከለ መንገድ እያቆዩ ያሉት የማህበረሰብ ክፍሎች ዕውቅና ቢሰጣቸው፣ ለጀፚረ የይዞታ ማረጋገጫ ቢዘጋጅለት፣ በጀፚረ ላይ ጥናቶች በስፋት ቢሰሩ፣ የህግ ማዕቀፍ ቢዘጋጅለት፣መንገድ ሲሰራ ዲዛይኑ ላይ የጉራጌ ባህላዊ ሸንጎ አባላት እንዲሳተፉና አስተያየት እንዲሰጡ ቢደረግ፣ መዋቅራዊ ጥበቃ ቢደረግለት፣ መሰረተ ልማቶች ሲገነቡ ቅንጅታዊ አሰራሮች ቢፈጠሩ የሚሉና ሌሎችም አስተያየቶች በምክክር መድረኩ ላይ ተነስተዋል፡፡ በመጨረሻም የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች በቸሀ ወረዳ፣ በፈረዝዬ ቀበሌ አንዛናባጥ በተሰኘ መንደር ተገኝተው የችግኝ ተከላ አከናውነዋል፡፡

ቅድመ ገጽ

ስለ እኛ

የተማሪዎች ቅበላ

መማር ማስተማር

ምርምር

አገልግሎት

ተማሪዎች

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማሕበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር “Training on improving first aid support and injury prevention for teachers ,students and sport professionals” በሚል ርዕስ ያዘጋጀው ስልጠና ተሰጠ

Read more ...
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀውና በጉራጌ ዞን ስር በሚገኙ የመንግስት ሆስፒታሎች በነርሲንግ ሙያ ላይ ተሰማርተው ለሚያገለግሉ ባለሙያዎች “Improving Nursing Care Service through Timely ,Purposive and Integrated Nursing Round ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና ተሰጠ፡፡

Read more ...
በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለማህበረሰብ አገልግሎት የሚውል የተቀናጀ የዓሳ፣ ዶሮ እና የጓሮ አትክልት ልማት ስራ የርክብክብ መርሀ ግብር እና በዋቤ ችግኝ ጣቢያ ለክረምት አረንጓዴ ልማት የሚውሉ ችግኞች ዝግጅት የመስክ ምልከታ ተካሄደ

Read more ...
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ለሚገኙ ከ600 በላይ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የደብተር እና የእስክሪፕቶ ድጋፍ አደረገ

Read more ...
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስዊዘርላንድ ሀገር ከሚገኘው የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ ከሆነው Lucerne University of Applied Sciences ጋር ስልጠና ላይ መሰረት ያደረገ የተማሪዎች ለውውጥ ( Students Exchange) አደረገ

Read more ...
በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተከናወነ ያለው የችግኝ ተከላ በምሁር አክሊል

Read more ...

Competency Based Exit Exam Preparation & Implementation” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ስልጠና ለኮምፒዊቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ መምህራን ተሰጠ ፡፡

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በወልቂጤ ዩኒቪርሲቲ በአስ/ኮ/ማ/ም/ፕ/ጽ/ቤት በተማሪዎች ዲን ስር በሚገኘው የስፖርትና መዝናኛ ቢሮ አማካይነት ተዘጋጅቶ ከመጋቢት 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ሲካሄድ የቆየው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ለውስጥ ስፖርታዊ ውድድር በዛሬው ዕለት ግንቦት 12/2015 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ፍፃሜውን አግኝቷል ፡፡

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው “የተሽከርካሪ አያያዝና አጠቃቀም የውስጥ አሰራር ስርዓት መመሪያ” ዙሪያ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አሽከርካሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ሰራተኞች፣ የየኮሌጆች መምህራን እና ተማሪዎች አመታዊ የልዩ ልዩ ስፖርት ውድድር መካሄድ ጀመረ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሶስት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የክበባት እና ማህበራት የስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ

በመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ፣ በሰው ሀብት ልማት መመሪያ እና ደንብ ፣ በግዢ ሂደት አፈጻጸም ፣ በንብረት አስተዳደርና በፋይናንስ መመሪያ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ለዩኒቨርሲቲው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ፣ ቡድን መሪዎችና አስተባባሪዎች በመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ፣ በሰው ሀብት ልማት መመሪያ እና ደንብ ፣ በግዢ ሂደት አፈጻጸም ፣ በንብረት አስተዳደርና በፋይናንስ መመሪያ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

We have 431 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2023. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT