ክፍት የሥራ ቦታ

የፈተና ጥሪ ቁጥር ሰባት(7)

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመምህራንና የላብ ቴክኒሺያን ለመቅጠር በቀን 17/03/2015 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ የተመዘገባችሁና ቅድመ ምልመላ ያለፋችሁ አመልካቾች ከዚህ በታች

Read more ...

የፈተና ጥሪ ቁጥር ስድሰት (6)

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኢንተርፕራይዝ በክፍት ሥራ መደቦች በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ለፈተና የሚቀርቡ ተፈታኞች ዝርዝር

የፈተና ቀን 05/05/2015 ሠዓት ከጠዋቱ 3:00

Read more ...

የፈተና ጥሪ ቁጥር አምስት (5)

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኢንተርፕራይዝ በክፍት ሥራ መደቦች በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ለፈተና የሚቀርቡ ተፈታኞች ዝርዝር

የፈተና ቀን 02/05/2015 ሠዓት ከጠዋቱ 3:00

Read more ...

ማስታወቂያ

ለሪሚዲያል (REMEDIAL) ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የሪሚዲያል (REMEDIAL)  ትምህርት ፈላጊዎችን ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

Read more ...

ለሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዳይሬክቶሬት በሥሩ ባሉት በCISCO እና በHuawei ዓለም አቀፍ አካዳሚዎቹ አማካኝነት ሥልጠናዎችን በማታ እና በሳምንቱ መጨረሻ (ቅዳሜና እሑድ) መርሐ ግብር በአነስተኛ ክፍያ ለመሥጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለዚህ ከዩኒቨርሲቲው ውጭ ያላችሁ የማኅበረሰብ አካላት በመመዝገብ ሥልጠናው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Read more ...

ማስታወቂያ

ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ነባር ቅድመ ምረቃ እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ

Read more ...

 

የዩኒቨርሲቲው የሴቶች ህጻናት እና ወጣቶች ኤች.አይ.ቪ ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ከተማሪዎች ህብረት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ47ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች-8) “ፈጠራና ቴክኖሎጂ ለጾታ እኩልነት” በሚል መሪ ቃል በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ተከብሯል፡፡

ፕሮግራሙን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የሴቶች ህጻናት እና ወጣቶች ኤች.አይ.ቪ ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ መሰረት አስራት ቀኑን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶች መብት መከበር ከመጀመሩ በፊት በጉራጌ ማህበረሰብ ዘንድ የሴቶች መብት ተሟጋች የነበረችው የቃቄ ውርድዎት ለሴቶች መብት መከበር ታደርግ የነበረውን ትግል እና የነበራትን ሚና አስመልክተው ለታዳሚዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡

ዳይሬክተሯ አያይዘውም ሴት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው በሚኖራቸው ቆይታ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች እንዴት መፍታት እንደሚችሉ የሚያግዙ የተለያዩ ስልጠናዎች እየተሰጣቸው እንደሚገኝ አስታውሰው ከመደበኛ የትምህርት ሰዓታቸው ውጪ የሚኖራቸውን ጊዜ ወደ ዜሮ ፕላን ማዕከል በመሄድ እንዲያሳልፉና የተለያዩ ተሞክሮዎችንና ልምዶችን የሚለዋወጡበትን መድረክ በአግባቡ እንዲጠቀሙ አሳስበዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርት የሆኑት መምህርት እስከዳር ተመራቂ ተማሪዎች በሚኖራቸው የመውጫ ፈተና( EXIT EXAM) ዙሪያ ለታዳሚዎቹ ሰፋ ያለ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በዕለቱም ከ8 ኮሌጆች እና ከ1 ትምህርት ቤት ከየትምህርት ክፍላቸው አብላጫ ውጤት ላመጡ ሴት ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የተቋሙ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ሴት ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ በመገንባት ላይ ያለው የህጻናት ማቆያ በፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ተጎብኝቷል፡፡

ለጥበብ እንተጋለን!

We Strive for Wisdom!

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

ቅድመ ገጽ

ስለ እኛ

የተማሪዎች ቅበላ

መማር ማስተማር

ምርምር

አገልግሎት

ተማሪዎች

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጉራጌ ዞን ለሚገኙ ከ600 በላይ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የደብተር እና የእስክሪፕቶ ድጋፍ አደረገ

Read more ...
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስዊዘርላንድ ሀገር ከሚገኘው የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ ከሆነው Lucerne University of Applied Sciences ጋር ስልጠና ላይ መሰረት ያደረገ የተማሪዎች ለውውጥ ( Students Exchange) አደረገ

Read more ...
በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተከናወነ ያለው የችግኝ ተከላ በምሁር አክሊል

Read more ...
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት ኮሚቴ አባላትና ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች እዣ ወረዳ ኔሸ ቀበሌ በመገኘት በአፈር መሸርሸር ምክንያት በተጎዱና በተራቆቱ ስፍራዎች ላይ የችግኝ ተከላ አከናወኑ፡፡

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኖሪያ ቤታቸው ለወደመባቸው ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ብዛታቸው 2100 የሆኑ የቤት ክዳን ቆርቆሮዎችንና 519 ፓኬት ሚስማር ድጋፍ አደረገ

Read more ...
ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ፣ የክልሉና የጉራጌ ዞን ዉሃና ማዕድን ኢነርጂ ተቋማት በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን በቸሀ ወረዳ በመገኘት የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ የሆኑ አርሶ አደሮችን የመስክ ምልከታ አካሄዱ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 175 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2023. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT