ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለማካካሻ ትምህርት (REMEDIAL) ከትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡትን ተማሪዎች ለመቀበል የመግቢያ ጊዜ ከየካቲት 29-30/2015 ዓ.ም መሆኑን አስቀድሞ ማስታወቁ ይታወቃል፡፡
በዚሁ መሰረት በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለማካካሻ ትምህርት (REMEDIAL) ከትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ተመድበው የመጡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መግባት የጀመሩ ሲሆን በሬጅስትራር፣ በኮሌጆች፣ በትምህርት ክፍሎች እና በተማሪዎች ህብረት አማካይነት ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ደማቅ የሆነ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል ::
ከትምህርት ሚኒስቴር ለማካካሻ ትምህርት (REMEDIAL) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት የተፈጥሮ ሳይንስና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር በድምሩ 2546 ሲሆን ተማሪዎቹ በነገው ዕለት ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቀው ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን በሰላም መጣችሁ እያልን ቆይታችሁ ያመረ እና የሰመረ እንዲሆን ከወዲሁ ልባዊ ምኞታችንን እንገልጻለን፡፡
ለጥበብ እንተጋለን!
We Strive for Wisdom!
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት