ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















 

የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት፣ የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ አባላት ፣ የጉራጌ ዞን ትራንስፖርት መምሪያ አባላት እና የጉራጌ ዞን ጸጥታ ዘርፍ በዛሬው ዕለት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በጋራ በመገናኘት የ2015 ዓም የ12ኛ ክፍል ፈተና ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ሰፊ የሆነ የጋራ ውይይት አካሂደዋል፡፡

የቅድመ ዝግጅቱን ሁኔታ አስመልክቶ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት ከዚህ ቀደም ለሁለት ተከታታይ ጊዜያት ዝግጅቱን መገምገማቸውን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል ገልጸዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲውን ዝግጅት አስመልክቶ ዶክተር ፋሪስ ደሊል ሲገልጹ በአካዳሚክ ዘርፍ የመፈተኛ ክፍሎችንና የተለያዩ ግብዓቶችን በማሟላት እንዲሁም በአስተዳደር ዘርፍ የምግብ ፣ የመኝታና የህክምና አገልግሎቶችን በማሟላት ረገድ ዝርዝር ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው ያሉትን ክፍተቶችን በመለየት ለቀጣይ ተገቢው ርብርብ ተደርጎ ተገቢው የእርምት ርምጃ መውሰድ እንደሚገባ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

በዞኑ በኩል በትራንስፖርት አቅርቦት ረገድ የተደረገውን ዝግጅትና የተፈታኝ ተማሪዎችን ስም ዝርዝርና መለያ ቁጥር አስቀድሞ በመለየት ለዩኒቨርሲቲው መቅረብ እንደሚገባው ተገልጿል፡፡ የጸጥታም ሁኔታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንደሚገባውም በውይይቱ ላይ ተብራርቷል፡፡

ተማሪዎች በፈተናው ዕለት እንዳይረበሹና ከመኖሪያ ስፍራቸውም ሲንቀሳቀሱ መንጠባጠብ ሳይኖር በተቀናጀ ሁኔታ ለማስኬድ እንዲረዳ በወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት በኩል ለርዕሣነ መምህራን ገለጻ ቢሰጥና በተመሳሳይም ርዕሳነ መምህራንም ተማሪዎችን በማሰባሰብ ተገቢውን ገለጻ እንዲሰጡ ለመግባባት ተችሏል፡፡

ወደ ዩኒቨርሲቲው የማድረጊያ ጊዜ ራቅ ያሉ አካባቢዎች ከመስከረም 26 የሚጀምር ሆኖ የተቀሩት መስከረም 27 እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ለሚዘገዩት እና በዩኒቨርሲቲ አቅራቢያ ላሉት መስከረም 28/2015 የመጨረሻው ቀን እንደሚሆን ተብራርቷል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የየወረዳዎቹና የየትምህርት ቤቶች የፈተና አስተባበሪዎች ተፈታኝ ተማሪዎችን እስከ ዩኒቨርሲቲው ድረስ አምጥተው የሚያሰረክቡበት መንገድ እንዲመቻች በሚል የውይይቱ ተሳታፊዎች በጋራ ተስማምተዋል፡፡

በመጨረሻም ተማሪዎቹ ወደ ተቋሙ ሲመጡ ይዘው መምጣት የተከለከሉ እና የተፈቀዱ ነገሮች አስመልክቶ በየትምህርት ቤቱ አማካይነት በሚደረግላቸው ገለጻ ላይ በቂ የሆነ ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ቢሰራ ወደዩኒቨርሲቲው ከመጡ በኋላ ተማሪዎቹ ላይ ሊፈጠር የሚችል እንግልት እንደማይኖር ተገልጿል፡፡

ከውይይቱ በኋላ የተደረገውን አጠቃላይ ዝግጅት አስመልክቶ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት፣ የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ አባላት ፣ የጉራጌ ዞን ትራንስፖርት መምሪያ አባላት እና የጉራጌ ዞን ጸጥታ ዘርፍ ተዟዙረው ጎብኝተዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የካውንስል አባላት በዩኒቨርሲቲው የ2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ዙሪያ ተወያዩ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 653 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT