ክፍት የሥራ ቦታ

ማስታወቂያ

National Exit Model Examination Schedule

National Exit Model Examination Schedule of Examinees assigned in Wolkite University. Students who need account activation can go to Central Library starting from tomorrow  morning

Read more ...

ማስታወቂያ

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ፣

Read more ...

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በ2016 ዓ.ም በሀገር-አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን Graduate Admission Test (GAT) መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ትምህርት ሚኒስቴር በወሰነው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ማለፋችሁን ያረጋገጣችሁ

Read more ...
















የኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር የሆኑት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ከትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ከሆኑት ከክቡር ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ጋር በጋራ በመሆን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ከውይይቱ አስቀድሞ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የአረንጓዴ አሻራቸውን ያኖሩ ሲሆን ከዚህም ክንውን በኋላ ዶክተር ፋሪስ ደሊል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የተቋሙን አጠቃላይ ሁኔታ የሚገልጽ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

በውይይቱም ወቅት እንደተገለጸው የልኡካን ቡድኑ ከዚህ ቀደም 23 ዩኒቨርሲቲዎችን በተመሳሳይ ሁኔታ መጎብኘታቸውን ገልጸዋል ፡፡ ውይይቱ በመሰረታዊነት ያተኮረው በሀገራችን ላይ የሚታየውን የትምህርት ጥራት ችግር መሰረት ባደረገ መልኩ ሲሆን በኢትዮጵያ ያለው የትምህርት ጥራት ችግር አሳሳቢ መሆኑን ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እና በተካሄደው ውይይት ላይ የተገኙት ተሣታፊዎችም ገልጸዋል።ችግሩ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተንሰራፋ እንድሆነ ጥናቶችን በመጥቀስ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በዝርዝር ገልጸዋል። ፕሮፌሰር ብርሀኑ አያይዘውም ሲገልጹ የኢትዮጵያን የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ

በሚደረገው ጥረት ከ2015 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አንዱ የመፍትሄ አካል ሆኖ የሚቀጥል እንደሚሆን በውይይቱ ላይ በአፅንኦት አንስተዋል፡፡

ሚኒስትሩ እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት ውስጥ የትምህርት ሥርዓቱ በተጨባጭ ያለበት ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ከመሆኑ አንጻር የተለያዩ ጥናቶችንና ውይይቶችን በማካሄድ አራት ዋና ዋና ችግሮችን መለየት ተችሏል ብለዋል፡፡ ለትምህርት ሥርዓቱ መውደቅ መሠረታዊ ከሆኑ ችግሮች መካከል፡- የትምህርት ጥራት ችግር፣ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት፣ የትምህርትና የክልልተኝነት መያያዝ እና የሞራል ኪሣራ መሆናቸውን ጠቁመው በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም በቀጣይ አዲስ ዩኒቨርሲቲዎችን የመክፈትና የማስፋፊያ ግንባታዎች የማካሄድ ዕቅድ የሌለ ሲሆን በሂደት ላይ ያሉ ግንባታዎችን የማስጨረስ፣ ያለውን ግብዓት የማሻሻልና ጥራት የማስጠበቅ ሥራ ላይ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከታችኛው የክፍል ደረጃ ጀምሮ መሥራት ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ ባሳለፍነው የትምህርት ዘመን የፈተና ደኅንነትን ለማስጠበቅ ፈተናውን በታብሌት ለመስጠት ሙከራ የተደረገ መሆኑን አስታውሰው በወቅቱ ከገጠመው የበጀት እጥረት የተነሳ ሳይተገበር መቅረቱን ገልጸው በቀጣይ ኩረጃን በማስቀረት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናቸውን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው እንዲፈተኑ ከወዲሁ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም ዩኒቨርሲቲዎች ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የእውነትና የእውቀት ምንጭ እንዲሆኑ ለማስቻል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስተዳደር ቦርድ አወቃቀር ጀምሮ ያለው ሥርዓት ሁሉን ባማከለ መልኩ መደራጀቱን እና በቅርብም ተግባራዊ እንደሚደረግ የጠቆሙት ሚኒስትሩ ሁሉም ባለድርሻዎች በጋራ ለለውጥና የተሻለ ትውልድ ለማፍራት እንዲተጉ ከአደራ ጭምር አሳስበዋል፡፡

ከተሰብሳቢዎች የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄዎች ክቡር አቶ መሀመድ ጀማል የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ዶክተር ፋሪስ ደሊል፣ክቡር ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌና ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በተለይም ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የሰጡት ማብራሪያ እጅግ ማራኪ፣ተዝናኖት የተሞላበት፣መሳጭና ትምህርት አዘል ሆኖ መልዕክቶችን እያዋዙ ያቀረቡበት ዘዴ በእጅጉ የተዋጣለት ነበር፡፡ በመጨረሻም የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳደር እያስገነባ ያለውን አዳሪ ትምህርት ቤት ተዟዙረው ጎብኝተዋ።

 

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ 13ኛ ዓመት አስመልክቶ “ የዓባይ ዘመን ትውልድ “ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የስነ-ጽሁፍ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት አባላት የዋቤ የንግድና የማማከር ስራዎች ኢንተርፕራይዝ የፈረዝየ የአቮካዶ እርሻን እና የምርምር ጣቢያ የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

Read more ...

በ2016 የትምህርት ዘመን ለማማካሻ ትምህርት (Remedial) ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ወደ ተቋሙ መግባት ጀምረዋል

Read more ...

Public Lecture has been held at Wolkite University

Read more ...

በ2015 ዓ.ም. በመውጫ ፈተና (Exit Exam) ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ባለድርሻ አካላት እውቅና ተሰጠ

Read more ...

“የባህር በር ጥያቄ የፖለቲካ ወይስ የህልውና ጥያቄ ? “ በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሴሚናር በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Read more ...

ዩኒቨርሲቲያችን በአገር አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀው የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እያከናወነ ያለውን ተስፋ ሰጪ ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት የትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዢን ቡድን አሳሰበ

Read more ...

Announcement for Test Takers of National Graduate Admission Test (GAT)

Read more ...

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የካውንስል አባላት በዩኒቨርሲቲው የ2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ዙሪያ ተወያዩ

Read more ...

የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች በዩኒቨርሲቲ ደረጃ በመገምገም ላይ ይገኛሉ

Read more ...

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኘው የጨቅላ ሕጻናት የእንክብካቤ ማዕከል እና የመምህራን መኖሪያ በሆነው አፓርታማ ግቢ ውስጥ የሚገኘው ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በይፋ ተመረቁ

Read more ...

በ2014 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ለመተግበር በዋቤ ችግኝ ጣቢያ የተዘጋጁት ችግኞችን አስመልክቶ የመስክ ጉብኝት ተካሄደ

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከጉራጌ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

Read more ...

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሁለት የስፔሻሊቲ የትምህርት ፕሮግራሞችን መስጠት ጀመረ

Read more ...

We have 778 guests and no members online

Wolkite University, P.O.Box 07, Wolkite, Guragie Zone, SNNPR, Ethiopia | +251-113-220042 | pird@wku.edu.et/president@wku.edu.et

Copyright © 2024. Wolkite University. Designed by Wolkite University ICT