ፕሮጀክቱ ሶስት መቶ ለሚሆኑ የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደረጋቸው ሲሆን ከዚህም አገልግሎት በተጨማሪ ከኢነርጂው በሚገኘው ተረፈ ምርት BIO SLURRY የተሰኘ ፈሳሽ የሆነ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች የተለያዩ ሰብሎችንና የጓሮ አትክልቶችን በማምረት እንዲጠቀሙ የሚያደርግ በመሆኑ ቴክኖሎጂው ዘርፈብዙ ጥቅሞችን የሚያስገኝ መሆኑን ጭምር ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም በአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለሚሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች አጠቃቀሙን በተመለከተ ስልጠና እንደሚሰጣቸው ከስምምነት ሰነዱ ላይ ለመረዳት ተችሏል፡፡